Skip to content
Facebook Twitter
Ethiopian Human Rights Commission – EHRC
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
        • Regions

          EHRC is an independent federal institution tasked with the promotion and protection of human rights in Ethiopia.

        • Addis Ababa
        • Afar
        • Amhara
        • Benishangul Gumuz
        • Gambella
        • Oromia
        • Somali
        • SNNP
        • Tigray
  • Areas of Work
        • Areas of Work

          We are an independent national human rights institution tasked with the promotion & protection of human rights in Ethiopia.

        • Economic, Social and Cultural Rights
        • Civil & Political Rights
        • IDPs, Refugees & Migrants Rights
        • Rights of Persons with Disabilities and the Rights of Older Persons
        • Women’s and Children’s Rights
        • HR Monitoring and Investigation
        • Human Rights Education
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • Events
  • Resources
 
Ethiopian Human Rights Commission – EHRCEthiopian Human Rights Commission – EHRC

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተ.መ.ድ.) ሁሉን-አቀፍ የግምገማ መድረክ (Universal Periodic Review) ላይ የሲቪል ማኅበራት ሚና ማጎልበት

June 5, 2022October 6, 2022 Press Release

የምክረ ሃሳቦች አፈጻጸምን የመከታተልና ሪፖርት የማቅረብ ተቀዳሚ ኃላፊነት የመንግሥት ቢሆንም ሲቪል ማኅበራት ይህንን አስመልክቶ የራሳቸውን ምልከታ ሪፖርት ለማቅረብ ልዩ ዕድል አላቸው

Twitter Facebook Telegram Email Whatsapp Print

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ጋዜጣዊ መግለጫ
ግንቦት 28 ቀን 2014 ዓ.ም.

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን በግንቦት 25 ቀን 2014 ዓ.ም.  የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤት ሁሉን-አቀፍ የግምገማ መድረክ (Universal Periodic Review) ምክረ ሃሳቦች አፈጻጸምን ከማስተዋወቅና ከመቆጣጠር አንጻር የሲቪል ማኅበራት ያላቸውን ሚና የተመለከተ ሁለተኛ ዙር ስልጠና አዘጋጅቷል። 

ሁሉን-አቀፍ የግምገማ መድረክ (Universal Periodic Review – UPR) በመንግሥታት የሚመራ፣ አሳታፊና በፍላጎት/ትብብር ላይ የሚመሰረት ሂደት ሲሆን፣ ሁሉም የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አባል ሀገራት በሀገራቸው ያለውን የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ለማሻሻል እና የሰብአዊ መብቶች ግዴታቸውን ለመወጣት የወሰዱትን እርምጃዎች በማስመልከት ሪፖርት እንዲያቀርቡ ዕድል የሚሰጥ ነው። የግምገማውን ሂደት ተከትሎ በግምገማው የተለዩ ክፍተቶችንና ጉድለቶችን ለማሻሻል ምክረ ሃሳቦች ይሰጣሉ። ኢትዮጵያ በሦስት የ UPR ዙሮች (2002፣ 2006 እና 2011 ዓ.ም.) ባቀረበችው ሪፖርት ላይ አስተያየት ተቀብላለች። በ2011 ዓ.ም. በተደረገው ግምገማ ላይ ከ132 ሀገራት 327 ምክረ ሃሳቦች ለኢትዮጵያ የቀረቡ ሲሆን፣ ከነዚህ መካከል ኢትዮጵያ 270 ምክረ ሃሳቦችን ተቀብላ 57ቱን ሳትቀበል ቀርታለች። 

ከጥቅምት 17 እስከ 18 ቀን 2014 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽንና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ጽሕፈት ቤት (Office of the High Commissioner for Human Rights) የሁሉን-አቀፍ የግምገማ መድረክ (Universal Periodic Review) ምክረ ሃሳቦች፣ እንዲሁም የተ.መ.ድ. የሰብአዊ መብቶች ተቋማት የሚሰጡትን ምክረ ሃሳቦች አፈጻጸም ከመቆጣጠር አንጻር የሲቪል ማኅበራት ያላቸውን ሚና የተመለከተ ስልጠና አዘጋጅተው ነበር። የክትትል ስብሰባውም ይህንን ስልጠና ተከትሎ የተካሄደ ሲሆን፣ ዓላማው የሲቪል ማኅበራትን የሁሉን-አቀፍ የግምገማ መድረክ (Universal Periodic Review) ምክረ ሃሳቦች አፈጻጸም የመከታተል አቅምን የበለጠ ማሳደግ እና ለመከታተል የወሰዷቸውን እርምጃዎች ከሲቪል ማኅበራት ለመስማት ነበር።

የኢሰመኮ የሴቶችና ሕፃናት መብቶች ኮሚሽነር መስከረም ገስጥ በመክፈቻ ንግግራቸው “የምክረ ሃሳቦች አፈጻጸምን አስመልክቶ መንግሥት ሪፖርት የማቅረብ ተቀዳሚ ኃላፊነት ያለው ቢሆንም የሲቪል ማኅበራት የምክረ ሃሳቦቹን አፈጻጸም አስመልክቶ የራሳቸውን ምልከታ ሪፖርት ለማቅረብ ልዩ ዕድል አላቸው” ሲሉ አስረድተዋል። ኮሚሽነሯ አክለውም የሲቪል ማኅበራት እና ብሔራዊ የሰብአዊ መብቶች ተቋማት በሀገራቸው ስላለው የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ተዓማኒነት ያለው መረጃ በመስጠት በመንግሥት እና በአህጉራዊ እንዲሁም ዓለም አቀፋዊ የሰብአዊ መብቶች ተቋማት መካከል ያለውን ክፍተት ለመሙላት እንደሚያግዙ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ የሲቪል ማኅበራት በተባበሩት መንግሥታት ሁሉን-አቀፍ የግምገማ መድረክ (Universal Periodic Review) ላይ ካላቸው ተሳትፎ ጋር በተገናኘ፤ በ2011 ዓ.ም. በተካሄደው የሦስተኛው ዙር የግምገማ ወቅት፣ እነዚሁ ማኅበራት የተቀናጀ ጥረት በማድረግ ወደ 10 የሚሆኑ ሪፖርቶችን አቅርበው እንደነበር ተገልጿል። የሲቪል ማኅበራት ልዩ ልዩ ተግዳሮቶች ቢኖርባቸውም ተግዳሮቶችን በመቋቋምና ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የሲቪል ማኅበራት አዋጅ መሻሻልን ተከትሎ ለኢትዮጵያ የሲቪል ማኅበራት የተፈጠረውን የበለጠ ምቹ ሁኔታዎች በመጠቀም  ከሌሎች ዓለም አቀፍ እና አህጉራዊ የሰብአዊ መብቶች ተቋማት ጋር በመተባበር ጭምር አስተዋጾአቸውን ሊያጎለብቱ እንደሚገባም ተገልጿል፡፡ 

በተጨማሪም የኢትዮጵያ የሲቪል ማኅበራት በአሁኑ ወቅት አገልግሎት ላይ ያሉ የሁሉን-አቀፍ የግምገማ መድረክ (Universal Periodic Review) የመረጃ ቋቶችን በመጠቀም እንደ ኢሰመኮ፣ የተ.መ.ድ. የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ጽሕፈት ቤት (Office of the High Commissioner for Human Rights) እና የብሔራዊ የሰብአዊ መብቶች የድርጊት መርኃ ግብር ጽሕፈት ቤትን (National Human Rights Action Plan Office) ከመሰሉ እና ድጋፍ ሊሰጡ ከሚችሉ ተቋማት ጋር ተቀራርበው እንዲሰሩ ምክረ ሃሳብ ቀርቧል። በስብሰባው የሲቪል ማኅበራት የሁሉን-አቀፍ የግምገማ መድረክ (Universal Periodic Review) ምክረ ሃሳቦች አፈጻጸምን በተመለከተ ሪፖርት እንዲያቀርቡ የሚያስችል እንዲሁም ተጨባጭ ውጤቶች እና የጊዜ ሰሌዳዎችን የሚያካትት ረቂቅ-እቅድ ተነድፏል። 

የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ጽህፈት ቤት ዳይሬክተር አልባብ ተስፋዬ በመዝጊያ ንግግራቸው፣ “ኢሰመኮ የኢትዮጵያን የሲቪል ማኅበራት የተባበሩት መንግሥታት ሁሉን-አቀፍ የግምገማ መድረክን ምክረ ሃሳቦች አፈጻጸም ለመከታተል እንዲሁም ከዓለም አቀፍ እና አህጉራዊ የሰብአዊ መብቶች ተቋማት ጋር እንዲሰሩ ለማገዝ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ ይቀጥላል” ብለዋል።


Location Addis Ababa

Reports & Press Releases

February 3, 2022February 6, 2022 Press Release
Stakeholders Consultation to Support the Implementation of the Recommendations of the Joint Investigation Report of EHRC and OHCHR on the Tigray Conflict
December 7, 2021December 7, 2021 Press Release
EHRC thanks its stakeholders for their support in its success in obtaining “A” status reaccreditation
August 26, 2021February 20, 2022 ጋዜጣዊ መግለጫ
ምስራቅ ወለጋ፡ የነዋሪዎችን ደኅንነት ለማረጋገጥ የአካባቢው የፀጥታ ኃይል ሊጠናከር ይገባል
December 10, 2021December 10, 2021 EHRC Quote
Join us and Stand Up for Human Rights on Human Rights Day

Signup for the Latest Update from EHRC

Submit your email to singup
Facebook Like us on FacebookTwitter Follow us on Twitter

Useful Links

  • NANHRI
  • GANHRI
  • OHCHR
  • ACHPR

Get Involved

  • Jobs
  • Events
  • Contact Us
  • Telegram Bot

Connect with Us

  • Facebook
  • Twitter
  • LinkedIn
  • YouTube
EHRC
We are an independent national human rights
institution tasked with the promotion & protection of
human rights in Ethiopia
Submit your email to get the latest update from EHRC

Address: Sunshine Tower No. 5, Meskel Square, on Bole Road next to Hyatt Regency Hotel, Addis Ababa, Ethiopia
Tel: +251115504031 | Fax: +251 11 550 4125 | PO Box 1165 Addis Ababa | Email: info@ehrc.org

© 2023 Copyright Ethiopian Human Rights Commission (EHRC). All Rights Reserved. Powered by 360Ground

We are using cookies to give you the best experience on our website.

You can find out more about which cookies we are using or switch them off in settings.

Scroll to top
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
    • Addis Ababa
    • Afar
    • Amhara
    • Benishangul Gumuz
    • Gambella
    • Oromia
    • Somali
    • SNNP
    • Tigray
  • Areas of Work
    • Economic, Social and Cultural Rights
    • Civil & Political Rights
    • IDPs, Refugees & Migrants Rights
    • Rights of Persons with Disabilities and the Rights of Older Persons
    • Women’s and Children’s Rights
    • HR Monitoring and Investigation
    • Human Rights Education
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Videos
    • Newsletters
    • Events
  • Resources
Facebook Twitter
Search
Ethiopian Human Rights Commission - EHRC
Powered by  GDPR Cookie Compliance
Privacy Overview

This website uses cookies so that we can provide you with the best user experience possible. Cookie information is stored in your browser and performs functions such as recognising you when you return to our website and helping our team to understand which sections of the website you find most interesting and useful.

Strictly Necessary Cookies

Strictly Necessary Cookie should be enabled at all times so that we can save your preferences for cookie settings.

If you disable this cookie, we will not be able to save your preferences. This means that every time you visit this website you will need to enable or disable cookies again.