Persons with disabilities (PwDs) in Ethiopia, face numerous challenges including lack of access to education, health care, employment, social protection, and discrimination due to attitudinal barriers prevalent in the community
ዲስሌክሲያ ያለባቸው ሰዎች የመማር እና እኩል ዕድል የማግኘት መብቶች ያሏቸው ቢሆንም አብዛኛዎቹ ሰብአዊ መብቶቻቸውን ለመጠቀም ትልቅ እንቅፋት ይገጥማቸዋል
ከጊዜ ወደ ጊዜ ቁጥራቸው እየጨመረ ያለው አረጋውያን ፍላጎታቸውን እና ሁኔታቸውን ያገናዘበ የሕግ እና የፖሊሲ ማእቀፍ በመዘርጋት ሰብአዊ መብቶቻቸውን ሙሉ በሙሉ እንዲጠቀሙ ማስቻል አስፈላጊ ነው
የምልክት ቋንቋን ይፋዊ የሥራ ቋንቋ ማድረግ መስማት የተሳናቸውን ሰዎች መረጃ የማግኘት መብት ለማረጋገጥ፣ በማኅበረሰብ ውስጥ በሁሉም ዘርፍ የሚኖራቸውን የተሳትፎ መጠንና የአገልግሎት ተደራሽነት ለማሳደግ ብሎም ሰብአዊ መብቶቻቸው ሙሉና ውጤታማ በሆነ ደረጃ እንዲረጋገጡ ለማስቻል አስፈላጊ ቅድመ ሁኔታ ነው
በኢትዮጵያ ስምምነቱ ተግባራዊ እንዲሆን የሚመለከታቸውን ባለድርሻ አካላት በማሳተፍ የማስፈጸሚያ ሕግ ሊወጣለት ይገባል
ከኢትዮጵያ የብሔር ብዝኃነት አንጻር ተጨማሪ ቋንቋዎችን በሥራ ቋንቋነት ለማካተት የሚያስችል የቋንቋ ፖሊሲ በቀረጻ ሂደት ላይ መሆኑ ቢታወቅም፤ መስማት ለተሳናቸው ሰዎች የግድ አስፈላጊ የሆነውን የምልክት ቋንቋን የሥራ ቋንቋ ለማድረግ በቂ ትኩረት አላገኘም
ይህን ውስን ሃብት ብሎም ዘርፉን የሚያስተዳድር የሕግና የፖሊሲ ማዕቀፍ ያስፈልጋል፡፡ ነፃነቱ የተጠበቀ ተቋም ማደራጀት፣ ግልጽና ገለልተኛ የፈቃድ አሰጣጥና እድሳት ሥርዓት መዘርጋት፣ ባለቤትነትንና ብዝኃነትን መወሰን፣ የይዘት ክትትል ሥርዓትን መደንገግ፣ የፕሮግራም ደረጃ ማስቀመጥ ያስፈልጋል
HRE is a key long-term strategy for addressing the underlying causes of human rights violations, preventing human rights abuses, combating discrimination, promoting equality and enhancing participation
በዚህና በተያያዥ ጉዳዮች ላይ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ከአማራ ክልል የመንግሥትና መንግሥታዊ ካልሆኑ ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ከመጋቢት 19 እስከ 20 ቀን 2014 ዓ.ም. ድረስ ሰፊ ውይይት አድርጓል
የሰብአዊ መብቶችን በማስከበር ረገድ ሚና ያላቸው የሰብአዊ መብቶች ተቋማት እንዲሁም በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ የሚሠሩ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማትም በሴት የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ላይ የሚፈጸሙ የመብት ጥሰቶች ላይ መረጃ የመሰብሰብ፣ የክትትል ሥራዎች እና ጥሰቶችን የማጋለጥ ሥራዎች መስራት አለባቸው።