የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከሰኔ ወር 2015 ዓ.ም. እስከ ሰኔ ወር 2016 ዓ.ም. ያለውን ጊዜ የሚሸፍነውን 3ተኛው የኢትዮጵያ ዓመታዊ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ሪፖርት ይፋ አድርጓል፡፡ ሪፖርቱ በኢሰመኮ የትኩረት ዘርፎች (Thematic Areas) የተለዩ ቁልፍ እመርታዎችን፣ ዋና ዋና አሳሳቢ ጉዳዮችን፣ ምክረ ሐሳቦችን እንዲሁም ልዩ ትኩረት የሚሹ የሰብአዊ መብቶች ጉዳዮች አካትቷል። ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 6/2015 አተገባበር...