Skip to content
Facebook Twitter
Ethiopian Human Rights Commission – EHRC
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
        • Regions

          EHRC is an independent federal institution tasked with the promotion and protection of human rights in Ethiopia.

        • Addis Ababa
        • Afar
        • Amhara
        • Benishangul Gumuz
        • Gambella
        • Oromia
        • Somali
        • SNNP
        • Tigray
  • Areas of Work
        • Areas of Work

          We are an independent national human rights institution tasked with the promotion & protection of human rights in Ethiopia.

        • Economic, Social and Cultural Rights
        • Civil & Political Rights
        • IDPs, Refugees & Migrants Rights
        • Rights of Persons with Disabilities and the Rights of Older Persons
        • Women’s and Children’s Rights
        • HR Monitoring and Investigation
        • Human Rights Education
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • Events
  • Resources
 
Ethiopian Human Rights Commission – EHRCEthiopian Human Rights Commission – EHRC

ለሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች የሰብአዊ ድጋፍ እና ጥበቃ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት ሰብአዊ መብቶችን መሠረት ያደረጉ አሠራሮችን እንዲከተሉ ለማስቻል የሰብአዊ መብቶች ትምህርትና ስልጠና ሥራዎች መጠናከር ፋይዳቸው የጎላ ነው

January 2, 2023January 2, 2023 Event Update

ከመኖሪያ ቀያቸው የተፈናቀሉ ሰዎች ለአደጋ የተጋለጡ እና ብዙውን ጊዜ ለመብቶቻቸው መከበር የተለየ ድጋፍ እና ጥበቃ ካልተደረገ ለተጨማሪ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት የመዳረጋቸው ዕድል የሰፋ ነው

Twitter Facebook Telegram Email Whatsapp Download Print

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በሱማሌ ክልል ለሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች አገልግሎት ከሚሰጡ መንግሥታዊ እና መንግሥታዊ ካልሆኑ ተቋማት ለተውጣጡ የሥራ ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች ከታኅሣሥ 17 እስከ 21 ቀን 2015 ዓ.ም. በድሬዳዋ ከተማ ስልጠና ሰጠ፡፡

ኢሰመኮ ከሰኔ 2013 ዓ.ም. እስከ ሰኔ 2014 ዓ.ም. ድረስ ያለውን ጊዜ የሚሸፍን የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ዓመታዊ ሪፖርት ይፋ ባደረገበት ወቅት የሶማሌ ክልል እ.ኤ.አ. ከ2022 – 2025 በሥራ ላይ የሚውል የዘላቂ መፍትሔ ስትራቴጂ ሰነድ መቅረጹ በክልል ደረጃ ለተፈናቃዮች የዘላቂ መፍትሔ ለማመቻቸት ምቹ አጋጣሚ የሚፈጥር በመሆኑ የተፈናቃዮችን የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ከማሻሻል አንጻር እንደመልካም ተሞክሮ እንደሚመለከተው መጥቀሱ የሚታወስ ነው። የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችን ሰብአዊ መብቶች መጠበቅና ሁኔታቸውን ማሻሻል ብሔራዊ ቁርጠኝነት የሚሻ እና የሁሉንም ባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ተሳትፎ እና ርብርብ የሚጠይቅ ነው። 

ስልጠናውም በዋናነት መንግሥታዊ በሆኑና መንግሥታዊ ባልሆኑ አገልግሎት ሰጪ ተቋማቶች ውስጥ የሚሠሩ ሠራተኞች እና የሥራ ኃላፊዎች በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ያላቸውን ዕውቀት ለማጎልበት ያለመ ነበር፡፡ እንዲሁም ተሳታፊዎች መሠረታዊ የሆኑ የሰብአዊ መብቶች እሴቶች በተለይም ሰብአዊ ክብር፣ እኩልነት፣ አድሎ አለመፈጸም እና ፍትሐዊነት ከአገልግሎት ሰጪዎች ተግባር ጋር ያላቸውን ትስስር በተመለከተ የተሳታፊዎችን ዕውቀት እና አመለካከት ለማዳበር የሚያስችሉ ክንውኖችን ያካተተ ነበር፡፡

የስልጠናው ተሳታፊዎች የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች በቅድመ መፈናቀል፣ መፈናቀል እና ድኅረ መፈናቀል ወቅት በዓለም-አቀፍ፣ አህጉራዊ እና ብሔራዊ የሕግ ማዕቀፎች ስለተሰጧቸው መብቶች፣ ከሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ጋር በተያያዘ የመንግሥት ግዴታዎች እና መንግሥታዊ ያልሆኑ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ኃላፊነትን በተመለከተ ያላቸውን ግንዛቤ ለማሳደግ ስልጠናው ምቹ አጋጣሚን ፈጥሯል።  

በተለይም ከምዝገባ እና ሰነድ ማግኘት፣ የሰብአዊ ድጋፍ በቂነት፣ የተፈናቃዮች ደኅንነት፣ ተጋላጭ ለሆኑ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ልዩ ጥበቃ እና ድጋፍ ማድረግ፣ ውጤታማ የሆነ ዘላቂ መፍትሔ ከማፈላለግ እንዲሁም ሰብአዊ መብቶችን መሠረት ያደረገ አገልግሎት አሰጣጥን ተግባራዊ ከማድረግ ጋር በተገናኘ የሚታዩ አሳሳቢ የሰብአዊ መብቶች ጉዳዮችን ለመለየት እና ተግባራዊ እርምጃ ለመውሰድ የሚያስችላቸውን ስልት የመንደፍ ክህሎት በስልጠናው በተግባር እንዲለማመዱ ለማድረግ ተችሏል፡፡ 

በስልጠናው ወቅት  ተሳታፊዎች ከመኖሪያ ቀያቸው የተፈናቀሉ ሰዎች ለአደጋ የተጋለጡ እና ብዙውን ጊዜ ለመብቶቻቸው መከበር የተለየ ድጋፍ እና ጥበቃ ካልተደረገ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ተጎጅ እንደሚሆኑ መገንዘባቸውን እና በዕለት ተዕለት አገልግሎት አሰጣጣቸው በስልጠናው ያገኙትን የሰብአዊ መብቶች ዕውቀት፣ አመለካከት እና ክህሎት በመጠቀም ተግባራዊ እርምጃ ለመውሰድ ያላቸውን ተነሳሽነት ገልጸዋል፡፡

Reports & Press Releases

July 14, 2022October 6, 2022 Event Update
በኢሰመኮ የክልል ከተሞች ጽሕፈት ቤቶች በሰኔ ወር ከተካሄዱ ዝግጅቶች በጥቂቱ
November 14, 2022November 14, 2022 EHRC on the News
የሴቶችና የሕፃናት ሰብአዊ መብቶች ዓመታዊ ሪፖርት ምን ይላል? – Addis Admass News
November 7, 2022November 9, 2022 Human Rights Concept
የሕፃናት ሰብአዊ መብቶች ጥበቃ እና ግጭት
October 21, 2022October 21, 2022 Event Update
National Human Rights Institutions (NHRIs) are key to tackle Business and Human Rights issues in the African continent

Signup for the Latest Update from EHRC

Submit your email to singup
Facebook Like us on FacebookTwitter Follow us on Twitter

Useful Links

  • NANHRI
  • GANHRI
  • OHCHR
  • ACHPR

Get Involved

  • Jobs
  • Events
  • Contact Us
  • Telegram Bot

Connect with Us

  • Facebook
  • Twitter
  • LinkedIn
  • YouTube
EHRC
We are an independent national human rights
institution tasked with the promotion & protection of
human rights in Ethiopia
Submit your email to get the latest update from EHRC

Address: Sunshine Tower No. 5, Meskel Square, on Bole Road next to Hyatt Regency Hotel, Addis Ababa, Ethiopia
Tel: +251115504031 | Fax: +251 11 550 4125 | PO Box 1165 Addis Ababa | Email: info@ehrc.org

© 2023 Copyright Ethiopian Human Rights Commission (EHRC). All Rights Reserved. Powered by 360Ground

We are using cookies to give you the best experience on our website.

You can find out more about which cookies we are using or switch them off in settings.

Scroll to top
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
    • Addis Ababa
    • Afar
    • Amhara
    • Benishangul Gumuz
    • Gambella
    • Oromia
    • Somali
    • SNNP
    • Tigray
  • Areas of Work
    • Economic, Social and Cultural Rights
    • Civil & Political Rights
    • IDPs, Refugees & Migrants Rights
    • Rights of Persons with Disabilities and the Rights of Older Persons
    • Women’s and Children’s Rights
    • HR Monitoring and Investigation
    • Human Rights Education
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Videos
    • Newsletters
    • Events
  • Resources
Facebook Twitter
Search
Ethiopian Human Rights Commission - EHRC
Powered by  GDPR Cookie Compliance
Privacy Overview

This website uses cookies so that we can provide you with the best user experience possible. Cookie information is stored in your browser and performs functions such as recognising you when you return to our website and helping our team to understand which sections of the website you find most interesting and useful.

Strictly Necessary Cookies

Strictly Necessary Cookie should be enabled at all times so that we can save your preferences for cookie settings.

If you disable this cookie, we will not be able to save your preferences. This means that every time you visit this website you will need to enable or disable cookies again.