Skip to content
Facebook Twitter
Ethiopian Human Rights Commission – EHRC
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
        • Regions

          EHRC is an independent federal institution tasked with the promotion and protection of human rights in Ethiopia.

        • Addis Ababa
        • Afar
        • Amhara
        • Benishangul Gumuz
        • Gambella
        • Oromia
        • Somali
        • SNNP
        • Tigray
  • Areas of Work
        • Areas of Work

          We are an independent national human rights institution tasked with the promotion & protection of human rights in Ethiopia.

        • Economic, Social & Cultural Rights
        • Civil & Political Rights
        • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
        • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
        • Women’s and Children’s Rights
        • HR Monitoring & Investigation
        • Human Rights Education
        • Human Rights Film Festival
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • Events
  • Resources
 
Ethiopian Human Rights Commission – EHRCEthiopian Human Rights Commission – EHRC

በሶማሌ ክልል በሚገኙ ማረሚያ ቤቶች የታራሚዎችን የሰብአዊ መብቶች አያያዝ ሁኔታ ለማሻሻል ባለድርሻ አካላት የተጀመሩ ጥረቶችን ሊደግፉ ይገባል

October 17, 2022October 18, 2022 Event Update

መንግሥት የታራሚዎችን ሰብአዊ መብቶች በማክበር፣ በማስከበር እና በማሟላት ረገድ ቀዳሚ ኃላፊነት አለበት

Twitter Facebook Telegram Email Whatsapp Print

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በ2014 ዓ.ም. በሶማሌ ክልል ከሚገኙ ማረሚያ ቤቶች መካከል በአራት ዞኖች ውስጥ በሚገኙ ማረሚያ ቤቶች ላይ የሰብአዊ መብቶች አያያዝ ሁኔታ ላይ ክትትል አከናውኗል። በክትትሉ ታራሚዎችን እና የማረሚያ ቤቶች ኃላፊዎችን ቃለመጠይቅ በማድረግ፣ ውይይት እና አካላዊ ምልከታ በማከናወን ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ ማሳየት የሚችል መረጃ የማሰባሰብ ሥራ ሠርቷል፡፡ ኢሰመኮ በክትትሉ በለያቸው ግኝቶች እና ምክረ ሃሳቦች ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር  ጥቅምት 3 ቀን 2015 ዓ.ም. በጅግጅጋ ከተማ ውይይት አድርጓል፡፡ 

በውይይቱ ወቅት ከክልሉ ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን፣ ከተባባሩት መንግሥታት የአደገኛ መድኃኒት እና ወንጀል መከላከል ጽሕፈት ቤት የኢትዮጵያ ቢሮ፣ ከሴንተር ፎር ጀስቲስ፣ ከዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ እና ከክልሉ ምክር ቤት፣ የፍትሕ ቢሮ፣ የሰላምና ጸጥታ ቢሮ የተወጣጡ ተወካዮች ተሳትፈዋል፡፡ 

የሶማሌ ክልል ከዚህ ቀደም የማእከላዊ ማረሚያ ቤት (ጄል ኦጋዴን) እና የጎዴ ማረሚያ ቤት በመባል የሚታወቁ ሁለት ማረሚያ ቤቶች ብቻ ነበሩት። ሀገራዊ የፖለቲካ ለውጥ መደረጉን ተከትሎ ሰፊ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ይፈጸምበት የነበረው ጄል ኦጋዴን በመዘጋቱ በክልሉ ያሉትን ታራሚዎች በአግባቡ ለማስተናገድ መንግሥት 6 ተጨማሪ ማረሚያ ቤቶች እንዲከፈቱ አድርጓል፡፡

ኢሰመኮ በክትትሉ በሸፈናቸው ማረሚያ ቤቶች በታራሚዎች እና በማረሚያ ቤቶች አስተዳደር መካከል ጥሩ ግንኙነት መኖሩ፣ ድብደባ እና መሰል ኢሰብአዊ ጥቃቶች አለመኖር፣ አሳሳቢ የሆነ የታራሚ መጨናነቅ የሌለ መሆኑ፣ ተጨማሪ ማስፋፊያ ለማድረግ እና ያሉትን ማረሚያ ቤቶች ደረጃቸውን ለማሳደግ ጥረቶች መጀመራቸው፣ ታራሚዎች የሃይማኖት ነጻነት እና የማምለኪያ ቦታዎች ያላቸው መሆኑ በጠንካራ ጎን ተለይተዋል፡፡ 

በሌላ በኩል በክልሉ የሚገኙ ማረሚያ ቤቶች ለወጣት ጥፋተኞች እና ለሴቶች የተለየ በቂ የማቆያ ቦታ አለመኖሩ፣ ታራሚዎች በጥፋታቸው ደረጃ ተለያይተው የማይያዙ መሆኑ፣ በአንዳንድ ማረሚያ ቤቶች ያሉ ጤና ጣቢያዎች በቂ የመመርመሪያ መሣሪያ እና መድኃኒት አለመሟላት፣ የቀለም እና የሙያ ትምህርት ከመስጠት አንጻር ሰፊ ውስንነቶች ያሉባቸው መሆኑ እንዲሁም የመዝናኛ አገልግሎት አለመኖር ከተለዩ ክፍተቶች መካከል ተጠቃሽ ናቸው።

ከዚህም በተጨማሪ የጀረር እና የቀብሪደሃር ማረሚያ ቤቶች ከፖሊስ ጣቢያነት ወደ ማረሚያ ቤትነት የተለወጡ በመሆናቸው ሙሉ የማረሚያ ቤት አገልግሎት መስጠት የሚችሉበት ደረጃ ላይ ስላልሆኑ ማሻሻያ ሊደረግባቸው እንደሚገባ ተጠቅሷል፡፡

የኢሰመኮ የሰብአዊ መብቶች የክትትልና ምርመራ ሥራ ክፍል ሪጅናል ዳይሬክተር ኢማድ አብዱልፈታህ፤ የክልሉ መንግሥት እና የክልል የማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ከዚህ በፊት በማረሚያ ቤቶች ይታዩ የነበሩ ኢሰብአዊ አያያዞችን ለማስቀረት የወሰዷቸው እርምጃዎች አበረታች መሆናቸውን ገልጸዋል። አክለውም በክትትሉ የተለዩ በተለይም ከበጀት ጋር የተያያዙ ክፍተቶችን በሂደት ለመቅረፍ እየጨመረ የሚሄድ በጀት በመመደብ የተሻለ የታራሚዎች አያያዝ እንዲኖር መንግሥት ተጨማሪ ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል። በተጨማሪም በማረሚያ ቤቶች ላይ የሚሠሩ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት የክልሉ ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን እያደረገ ያለውን ጥረት እንዲደግፉ ምክረ ሃሳብ ሰጥተዋል፡፡

የክልሉ ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር በሺር አህመድ ሃሺ በበኩላቸው ማረሚያ ቤቶቹን በሚፈለገው ልክ ለማሻሻል የበጀት እጥረት ያለባቸው መሆኑን ጠቅሰው በኢሰመኮ የቀረቡ ምክረ ሃሳቦችን ተግባራዊ ለማድረግ በቁርጠኝት እንደሚሠሩ በማረጋገጥ በዚህ ረገድ ሁሉም አካላት የበኩላቸውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል፡፡

Location Somali

Related posts

September 28, 2022October 7, 2022 Human Rights Concept
The Human Right to Access to Information
August 23, 2022October 5, 2022 Human Rights Concept
አስገድዶ ከመሰወር የመጠበቅ ሰብአዊ መብት
July 13, 2022October 6, 2022 Event Update
Consultative meeting on monitoring and implementing the recommendations of United Nations human rights treaty bodies and the Universal Periodic Review
January 25, 2022February 20, 2022 Quiz
ስለ ትምህርት ሰብአዊ መብት ምን ያህል ያውቃሉ?

Signup for the Latest Update from EHRC

Submit your email to singup
Facebook Like us on FacebookTwitter Follow us on Twitter

Useful Links

  • NANHRI
  • GANHRI
  • OHCHR
  • ACHPR

Get Involved

  • Jobs
  • Events
  • Contact Us
  • Telegram Bot

Connect with Us

  • Facebook
  • Twitter
  • LinkedIn
  • YouTube
EHRC
We are an independent national human rights
institution tasked with the promotion & protection of
human rights in Ethiopia
Submit your email to get the latest update from EHRC

Address: Sunshine Tower No. 5, Meskel Square, on Bole Road next to Hyatt Regency Hotel, Addis Ababa, Ethiopia
Tel: +251115504031 | Fax: +251 11 550 4125 | PO Box 1165 Addis Ababa | Email: info@ehrc.org

© 2023 Copyright Ethiopian Human Rights Commission (EHRC). All Rights Reserved. Powered by 360Ground

We are using cookies to give you the best experience on our website.

You can find out more about which cookies we are using or switch them off in settings.

Scroll to top
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
    • Addis Ababa
    • Afar
    • Amhara
    • Benishangul Gumuz
    • Gambella
    • Oromia
    • Somali
    • SNNP
    • Tigray
  • Areas of Work
    • Economic, Social & Cultural Rights
    • Civil & Political Rights
    • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
    • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
    • Women’s & Children’s Rights
    • HR Monitoring & Investigation
    • Human Rights Education
    • Human Rights Film Festival
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Videos
    • Newsletters
    • Events
  • Resources
Facebook Twitter
Search
Ethiopian Human Rights Commission - EHRC
Powered by  GDPR Cookie Compliance
Privacy Overview

This website uses cookies so that we can provide you with the best user experience possible. Cookie information is stored in your browser and performs functions such as recognising you when you return to our website and helping our team to understand which sections of the website you find most interesting and useful.

Strictly Necessary Cookies

Strictly Necessary Cookie should be enabled at all times so that we can save your preferences for cookie settings.

If you disable this cookie, we will not be able to save your preferences. This means that every time you visit this website you will need to enable or disable cookies again.