Skip to content
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Ethiopian Human Rights Commission – EHRC
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
        • Regions

          EHRC is an independent federal institution tasked with the promotion and protection of human rights in Ethiopia.

        • Addis Ababa
        • Afar
        • Amhara
        • Benishangul Gumuz
        • Gambella
        • Oromia
        • Somali
        • Tigray
        • Central Ethiopia
        • Dire Dawa
        • Harari
        • Sidama
        • South Ethiopia
        • South West Ethiopia Peoples'
  • Areas of Work
        • Areas of Work

          We are an independent national human rights institution tasked with the promotion & protection of human rights in Ethiopia.

        • Economic, Social & Cultural Rights
        • Civil & Political Rights
        • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
        • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
        • Women’s & Children’s Rights
        • Human Rights Education
        • Human Rights Monitoring & Investigation
        • Human Rights Film Festival
        • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
 
Ethiopian Human Rights Commission – EHRCEthiopian Human Rights Commission – EHRC

የአካል ጉዳተኞች ሥራ የማግኘት መብት እንዲከበር የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል

June 3, 2022October 5, 2022 Event Update

የአካል ጉዳተኞች የሥራ ሥምሪት መብትን የሚመለከት አዋጅ የወጣ እና ሥራ ላይ የዋለ ቢሆንም፤ በተለያዩ የመንግሥት እና የግል ተቋማት ያለው ያልተጣጣመ አሠራር አካል ጉዳተኞች በሥራ ቅጥር፣ ዕድገት፣ ድልድል፣ ዝውውር፣ ሥልጠናና ሌሎች የሥራ ሁኔታዎች ወቅት መድልዎ እንዲደርስባቸው መንስኤ ነው

Twitter Facebook Telegram Email Whatsapp Print
Persons with disability

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከአማራ ክልል የአካል ጉዳተኞች ማኅበራት ፌዴሬሽን እና ከተለያዩ ዞኖች የተውጣጡ የዓይነ ሥውራን፣ የእንቅስቃሴ ጉዳት፣ መስማት የተሳናቸው እና የስጋ ደዌ ተጠቂዎች ማኅበራት ተወካዮች፣ የአካል ጉዳተኞች መብቶችን በተመለከቱ የሕግ ማዕቀፎች ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ከግንቦት 16 እስከ 18 ቀን 2014 ዓ.ም. በእንጅባራ ከተማ ሰጥቷል።

ለሦስት ተከታታይ ቀናት የቆየው ስልጠና ስለ ኢሰመኮ ስልጣንና ተግባር፣ የሰብአዊና የአካል ጉዳተኝነት መብቶች ጽንሰ-ሃሳብ፣ የአካል ጉዳተኞች መብቶችን በተመለከቱ ዓለም አቀፍ፣ አህጉራዊ እና ሀገር አቀፍ የሕግ ማዕቀፎች ዙሪያ ያተኮረ ሲሆን፤ እነዚህን ሕጎች ተግባራዊ በማድረግ ሂደት ውስጥ አካል ጉዳተኞች በዕለት ከዕለት ሕይወታቸው ውስጥ ከሚገጥሟቸው ዓይነተ-ብዙ መሰናክሎች አንጻር በማስተሳሰር የተሰናዳ ነበር።

ተሳታፊዎች በክልሉ የአካል ጉዳተኞችን የሥራ ሥምሪት እና የመሰረተ-ልማቶች ተደራሽነት መብትን በተመለከተ በማኅበረሰቡ፣ በመንግሥት፣ በአካል ጉዳተኞች ዘንድ የተንሰራፋ የግንዛቤ ክፍተት መኖሩን አንስተዋል። ማኅበራት ያልተደራጁባቸው የአካል ጉዳት ዓይነቶች (ለምሳሌ፡-የአዕምሮ እድገት ውስንነት) መኖራቸው፣ ማኅበራቱ ያላቸው የሰው ኃይል እና የገንዘብ አቅም ውስንነት፣ የውትወታ ሥራዎችን ለማከናወን ያሉ የግንዛቤ ክፍተቶች በተግዳሮትነት ተጠቅሰዋል።

የአካል ጉዳተኞች የሥራ ሥምሪት መብትን የሚመለከት አዋጅ የወጣ እና ሥራ ላይ የዋለ ቢሆንም፤ በተለያዩ የመንግሥት እና የግል ተቋማት ያለው ያልተጣጣመ አሠራር አካል ጉዳተኞች በሥራ ቅጥር፣ ዕድገት፣ ድልድል፣ ዝውውር፣ ሥልጠናና ሌሎች የሥራ ሁኔታዎች ወቅት መድልዎ እንዲደርስባቸው መንስኤ እንደሆነ በውይይት ወቅት ተመላክቷል። የሥራ ቅጥር ማስታወቂያዎች ለአካል ጉዳተኞች ተደራሽ አለመሆናቸው፣ የተመጣጣኝ ማመቻቸት ርምጃዎችን አለመውሰድ፣ ከትምህርት ዝግጅትና ከሥራ ልምዳቸው ውጪ በሆኑ የሥራ መደቦች መመደብ የመሳሰሉት ተግዳሮቶች መሮራቸውን የማኅበራቱ ተወካዮች ገልጸዋል። አክለውም እንደ ሕክምና፣ ትምህርት፣ ልዩ ልዩ የመንግሥት አገልግሎቶች፣ መንገድ፣ ፍርድ ቤት፣ ባንክ፣ የንግድ ተቋማት የመሳሰሉ መሰረታዊ አገልግሎት መስጫዎች ለአካል ጉዳተኞች በሚፈለገው መጠን ምቹ እና ተደራሽ አለመሆናቸው አንስተዋል።

የሥልጠናው ተሳታፊዎች እነዚህን እና መሰል የአካል ጉዳተኞች መሰናክሎች ለማስወገድ የሚረዱ ልዩ ልዩ እርምጃዎችን እንዲወስዱ ለፌዴራልና ለክልል ሕግ አውጪ ምክር ቤቶች፣ በየደረጃው ላሉ የሕግ አስፈጻሚ አካላት፣ ለፍርድ ቤቶች፣ ለኢሰመኮ እና ለመገናኛ ብዙኃን ልዩ ልዩ ምክረ ሃሳቦችን አቅርበዋል፡፡ ለዋቢነት ያክል በፌዴራል እና በክልል ሕግ አውጪ ምክር ቤቶች ለአካል ጉዳተኞች የተለዩ መቀመጫዎች እንዲኖራቸው፤ አካል ጉዳተኞች እና የአካል ጉዳተኞች ማኅበራት በተቋማት አደረጃጀት ክለሳ፣ በሕግና ፖሊሲ ዝግጅት ሂደቶች እና በመሳሰሉት አካል ጉዳተኞችን በቀጥታ በሚመለከቱ ጉዳዮች ላይ ንቁ እና ትርጉም ያለው ተሳትፎ እንዲያደርጉ እንዲደረግ የሚሉት የሚጠቀሱ ናቸው።

የሲቪል ሰርቪስ እና የግል ድርጅቶች የቅጥር፣ የትምህርትና ስልጠና ዕድሎች፣ የደረጃ ዕድገት እና ተያያዥ መመሪያዎች ከአካል ጉዳተኞች ሥራ ስምሪት መብት አንጻር ዳግም እንዲጤኑ እና መገናኛ ብዙኃን የአካል ጉዳተኞች መብቶች ግንዛቤ እንዲፈጥሩ የበኩላቸውን ሚና እዲጫወቱ በስልጠናው ላይ ጥሪ ቀርቧል። በበጎ ጎኑ ደግሞ በክልሉ የሚንቀሳቀሱ ልዩ ልዩ የአካል ጉዳተኞች ማኅበራት በክልል፣ በዞን እና በወረዳ ደረጃ የተዋቀሩ ሲሆን፤ የአካል ጉዳተኞች መብቶች እንዲከበሩ በርካታ ሥራ የሚሠሩ መሆናቸው ተጠቅሷል፡፡

በስልጠናው ማጠቃለያ ንግግር ያሰሙት የኢሰመኮ ባሕር ዳር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አለባቸው ብርሃኑ፣ “አካል ጉዳተኞች ለልዩ ልዩ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች ይበልጥ ተጋላጭ በመሆናቸው በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የዘርፍ ኮሚሽነር የተሰየመለት እና ጉዳዩን የሚመለከት ሥራ ክፍል በማደራጀት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ነው” ብለዋል። አክለውም ኮሚሽኑ ስለ አካል ጉዳተኝነት ያለውን የተሳሳተ ግንዛቤ ለማረም የሚረዱ የስልጠና እና የውትወታ፣ እንዲሁም የሰብአዊ መብቶች ክትትልና ምርመራ ሥራዎቹን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡

በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ የአካል ጉዳተኞች ማኅበራትን እና ፌዴሬሽኖችን አቅም ለማሳደግ የሚረዱ ልዩ ልዩ ስልጠናዎች፣ የገንዘብ እና የእውቀት ድጋፎች፣ ወጥ የሆነ አደረጃጀት እንዲኖራቸውና እርስ በርሳቸው በቅንጅት የመሥራት ልምድ እንዲያዳብሩ መግባባት ላይ ተደርሷል። በተጨማሪም ሰልጣኞችም በስልጠናው ያገኙትን ዕውቀት በየደረጃው ላሉ አባላቶቻቸው የማካፈል እና የአካል ጉዳተኞች መብቶችን የተመለከቱ ሕጎች በተግባር እንዲከበሩ ለማስቻል ሰፊ ሥራ የሚጠበቅባቸው መሆኑን አጽንዖት በመስጠት ስልጠናው ተጠናቋል፡፡

Related posts

July 11, 2023August 28, 2023 Event Update
በግንቦት እና በሰኔ ወር 2015 ዓ.ም. የተሰጡ የሰብአዊ መብቶች ስልጠናዎች
May 22, 2023May 22, 2023 Event Update
ኢሰመኮ ለፖሊስ አባላት፣ ለወጣቶች፣ ለሲቪክ ማኅበራት እና ለመንግሥት አገልግሎት ሰጪ አካላት የሰጣቸው የሰብአዊ መብቶች ትምህርት ስልጠናዎች
September 29, 2022October 5, 2022 Event Update
በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን በአካል ጉዳተኞች እና አረጋውያን መብቶች ዙርያ ለሚሠሩ የባለድርሻ አካላት የቀረበ የ2015 ዓ.ም. ዕቅድ ማስተዋወቅ እና አብሮ የመሥራት ጥሪ
February 7, 2023August 28, 2023 Event Update
የአካል ጉዳተኞች ማኅበራትን ዐቅም በሰብአዊ መብቶች ትምህርት በመገንባት የአካል ጉዳተኞችን ሰብአዊ መብቶች ተግባራዊ ማድረግ

Signup for the Latest Update from EHRC

Submit your email to singup
Facebook Like us on FacebookXFollow us on XYouTube Follow us on YouTubeLinkedin Follow us on LinkedinWhatsApp WhatsAppTikTok TikTokTelegram TelegramInstagram InstagramFlicker Flickr

Useful Links

  • NANHRI
  • GANHRI
  • OHCHR
  • ACHPR
  • TRANSITIONAL JUSTICE

Get Involved

  • Jobs
  • Events
  • Contact Us
  • Telegram Bot
  • Subscribe to our newsletter

Connect with Us

  • Facebook
  • Twitter
  • LinkedIn
  • YouTube
  • Flickr
  • Instagram
Descriptive Text

We are an independent
national human rights
institution tasked with
the promotion and protection of human
rights in Ethiopia.

Submit your email to get the latest update from EHRC

Address: Sunshine Tower No. 5, Meskel Square, on Bole Road next to Hyatt Regency Hotel, Addis Ababa, Ethiopia
Tel: +251115504031 | Fax: +251 11 550 4125 | PO Box 1165 Addis Ababa | Email: info@ehrc.org


The contents of this website, excepting third party content for which the Commission bears no responsibility,
may be freely used and copied for educational and other non-commercial purposes, provided that any such reproduction is accompanied by an acknowledgement of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC). Source of images used in the content of this website: EHRC Media and Communications Department Archive and Creative Common License.

This website is managed by the Media and Communications team of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC).

We are using cookies to give you the best experience on our website.

You can find out more about which cookies we are using or switch them off in .

Scroll to top
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
    • Addis Ababa
    • Afar
    • Amhara
    • Benishangul Gumuz
    • Central Ethiopia
    • Dire Dawa
    • Gambella
    • Harari
    • Oromia
    • Sidama
    • Somali
    • South Ethiopia
    • South West Ethiopia Peoples’
    • Tigray
  • Areas of Work
    • Economic, Social & Cultural Rights
    • Civil & Political Rights
    • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
    • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
    • Human Rights Monitoring & Investigation
    • Women’s & Children’s Rights
    • Human Rights Education
    • Human Rights Film Festival
    • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Search
Ethiopian Human Rights Commission - EHRC
Powered by  GDPR Cookie Compliance
Privacy Overview

This website uses cookies so that we can provide you with the best user experience possible. Cookie information is stored in your browser and performs functions such as recognising you when you return to our website and helping our team to understand which sections of the website you find most interesting and useful.

Strictly Necessary Cookies

Strictly Necessary Cookie should be enabled at all times so that we can save your preferences for cookie settings.

If you disable this cookie, we will not be able to save your preferences. This means that every time you visit this website you will need to enable or disable cookies again.