Skip to content
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Ethiopian Human Rights Commission – EHRC
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
        • Regions

          EHRC is an independent federal institution tasked with the promotion and protection of human rights in Ethiopia.

        • Addis Ababa
        • Afar
        • Amhara
        • Benishangul Gumuz
        • Gambella
        • Oromia
        • Somali
        • Tigray
        • Central Ethiopia
        • Dire Dawa
        • Harari
        • Sidama
        • South Ethiopia
        • South West Ethiopia Peoples'
  • Areas of Work
        • Areas of Work

          We are an independent national human rights institution tasked with the promotion & protection of human rights in Ethiopia.

        • Economic, Social & Cultural Rights
        • Civil & Political Rights
        • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
        • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
        • Women’s & Children’s Rights
        • Human Rights Education
        • Human Rights Monitoring & Investigation
        • Human Rights Film Festival
        • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
 
Ethiopian Human Rights Commission – EHRCEthiopian Human Rights Commission – EHRC

አዲስ አበባ፦ በማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መብቶች ላይ የተካሄደ ብሔራዊ የፖሊሲ ምክክር መድረክ 

September 5, 2024September 5, 2024 Event Update

የሽግግር ፍትሕ ሂደቱ እና ሀገራዊ የምክክር መድረኩ ለማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መብቶች በቂ ትኩረት በሚሰጥ መልኩ ተግባራዊ እንዲሆን ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን አስተዋጽዖ ሊያደርጉ ይገባል

Twitter Facebook Telegram Email Whatsapp Print

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሰብአዊ መብቶች ማእከል ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ የማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መብቶች አተገባበር ላይ ትኩረት ያደረገ ብሔራዊ የፖሊሲ ምክክር መድረክ ነሐሴ 22 እና 23 ቀን 2016 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ አካሂዷል። መድረኩ “በኢትዮጵያ የማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ መብቶች ግዴታዎችን የማክበር ሁኔታ፤ መሻሻል ወይስ ወደ ኋላ መመለስ?” (‘The Status of Compliance with Socio-economic Rights Obligations in Ethiopia – Progression or Regression?’) በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ሲሆን፣ የማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መብቶች ፖሊሲዎች፣ ክፍተቶችና ተግዳሮቶች እንዲሁም የመፍትሔ እርምጃዎች ላይ ያተኮረ ነበር። በምክክር መድረኩ የፌዴራል እና የክልል ምክር ቤቶች ተወካዮች፣ የትምህርት፣ የጤና እና የፕላንና ልማት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራን እና የትምህርት ማኅበረሰብ አባላት፣ የክልል ቢሮዎችን ጨምሮ የሌሎች መንግሥታዊ እና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት ተወካዮች ተሳትፈዋል።  

የኢሰመኮ ተጠባባቂ ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ ንግግር ሲያደርጉ

የምክክር መድረኩ በዋነኝነት የጤና፣ የመኖሪያ ቤት፣ የትምህርት፣ የሠራተኞች እንዲሁም የምግብ መብቶች ላይ ያተኮረ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ በማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መብቶች አተገባበር ላይ ያሉ ተግዳሮቶችን እና የፖሊሲ ክፍተቶችን መለየትን፤ የመብቶቹን ተፈጻሚነት ለማሻሻል የሚረዱ የመፍትሔ ሐሳቦችን ማቅረብን እንዲሁም በመንግሥት ተቋማት፣ በሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች እና በትምህርት ማእከላት መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር ሰብአዊ መብቶችን መሠረት ያደረገ የማኅበራዊ እና የኢኮኖሚያዊ መብቶችን አተገባበር ለማሻሻል ያለመ ነው።  

የኢሰመኮ የሲቪል፣ የፖለቲካ፣ የማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መብቶች ኮሚሽነር ዶ/ር አብዲ ጅብሪል ንግግር ሲያደርጉ

በምክክር መድረኩ ከኢሰመኮ፣ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም ከሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች በተውጣጡ የሥራ ኃላፊዎች፣ ምሁራን እና ባለሙያዎች ሰብአዊ መብቶችን መሠረት ያደረገ አቀራረብን፤ የመኖሪያ ቤት፣ የምግብ እና የሠራተኞች መብቶችን፤ የማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መብቶችን የተመለከቱ የመንግሥት ግዴታዎችን እንዲሁም የፖሊሲ እና አተገባበር ክፍተቶችን የተመለከቱ ጽሑፎች ቀርበዋል። በተጨማሪም የትምህርት እና የጤና መብቶች፣ የፖሊሲ እና የአተገባበር ደረጃን የሚያመላክቱ ጽሑፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።  

የኢሰመኮ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ መብቶች ሥራ ክፍል ዳይሬክተር ዶ/ር ብራይትማን ገብረሚካኤል ገለፃ ሲያደርጉ

የመድረኩ ተሳታፊዎች የማኅበራዊ እና የኢኮኖሚያዊ መብቶች የሕግ፣የፖሊሲ እና የአተገባበር ማዕቀፎችን ከማሻሻል አንጻር እየተወሰዱ ስላሉ እና በቀጣይ ሊወሰዱ ስለሚገባቸው እርምጃዎች ያነሱ ሲሆን፣ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መብቶችን ከሚመለከቱ ዓለም አቀፍ ስምምነቶች የሚመነጩ ግዴታዎችን ተፈጻሚነት በተመለከተ የፌዴራል እና የክልል ሕግ አውጪ እንዲሁም ፍትሕ ሚኒስቴርን ጨምሮ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ሕግ አስፈጻሚ አካላት የግዴታዎችን ተፈጻሚነት ለማረጋገጥ ሊወስዷቸው ስለሚገቡ እርምጃዎች እና በሂደቱም ታሳቢ ሊያደርጓቸው ስለሚገቡ ጉዳዮች ሐሳባቸውን ሰጥተዋል። በተጨማሪም፣ በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ የሚሠሩ የሲቪክ ማኅበረሰብ ድርጅቶች እና ሌሎች ጉዳዩ የሚመለከታቸው መንግሥታዊ እና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት ለዚህ የሰብአዊ መብቶች ዘርፍ በቂ ትኩረት በመስጠት ክትትላቸውን እንዲያጠናክሩ ሐሳብ ቀርቧል። 

የኢሰመኮ ተጠባባቂ ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ ንግግር ሲያደርጉ

የኢሰመኮ ተጠባባቂ ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ በሀገራችን ኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች ያለው ግጭት እና አለመረጋጋት፣ ድርቅ እና መሰል አደጋዎች ከሌሎች ክስተቶች ጋር ተዳምረው የማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መብቶች በተለይም የምግብ፣ የመኖሪያ ቤት፣ የትምህርት፣ የጤና እና የሥራ መብቶች በአሳሳቢ ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኙ ጠቁመዋል። አያይዘውም የሽግግር ፍትሕ ሂደቱ እና ሀገራዊ የምክክር መድረኩ ለማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መብቶች በቂ ትኩረት በሚሰጥ መልኩ ተግባራዊ እንዲሆን እንዲሁም ተገቢውና አስፈላጊው የፖሊሲ እና መዋቅራዊ ለውጦችን ለማምጣት ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን አስተዋጽዖ እንዲያደርጉ ጥሪ አድርገዋል።

Related posts

October 23, 2023October 27, 2023 Event Update
በብሔራዊ የንግድ እና ሰብአዊ መብቶች የድርጊት መርኃ ግብር ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር የተካሄደ ውይይት
December 20, 2023December 20, 2023 Event Update
ቴክኖሎጂ ለሰብአዊ መብቶች መከበር ያለውን ሚና ለኮሚሽኑ ባለሙያዎች ለማስገንዘብ የተዘጋጀ ስልጠና
August 8, 2024August 9, 2024 Event Update
በአሳሳቢ ሁኔታ ላይ የሚገኘውን ትምህርት የማግኘት መብት በተመለከተ የተካሄደ የምክክር መድረክ
January 3, 2024January 3, 2024 Event Update
ምግብ በማግኘት መብት እና ሰብአዊ መብቶችን መሠረት ያደረገ አቀራረብ ላይ የተሰጠ ስልጠና

Signup for the Latest Update from EHRC

Submit your email to singup
Facebook Like us on FacebookXFollow us on XYouTube Follow us on YouTubeLinkedin Follow us on LinkedinWhatsApp WhatsAppTikTok TikTokTelegram TelegramInstagram InstagramFlicker Flickr

Useful Links

  • NANHRI
  • GANHRI
  • OHCHR
  • ACHPR
  • TRANSITIONAL JUSTICE

Get Involved

  • Jobs
  • Events
  • Contact Us
  • Telegram Bot
  • Subscribe to our newsletter

Connect with Us

  • Facebook
  • Twitter
  • LinkedIn
  • YouTube
  • Flickr
  • Instagram
Descriptive Text

We are an independent
national human rights
institution tasked with
the promotion and protection of human
rights in Ethiopia.

Submit your email to get the latest update from EHRC

Address: Sunshine Tower No. 5, Meskel Square, on Bole Road next to Hyatt Regency Hotel, Addis Ababa, Ethiopia
Tel: +251115504031 | Fax: +251 11 550 4125 | PO Box 1165 Addis Ababa | Email: info@ehrc.org


The contents of this website, excepting third party content for which the Commission bears no responsibility,
may be freely used and copied for educational and other non-commercial purposes, provided that any such reproduction is accompanied by an acknowledgement of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC). Source of images used in the content of this website: EHRC Media and Communications Department Archive and Creative Common License.

This website is managed by the Media and Communications team of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC).

We are using cookies to give you the best experience on our website.

You can find out more about which cookies we are using or switch them off in .

Scroll to top
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
    • Addis Ababa
    • Afar
    • Amhara
    • Benishangul Gumuz
    • Central Ethiopia
    • Dire Dawa
    • Gambella
    • Harari
    • Oromia
    • Sidama
    • Somali
    • South Ethiopia
    • South West Ethiopia Peoples’
    • Tigray
  • Areas of Work
    • Economic, Social & Cultural Rights
    • Civil & Political Rights
    • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
    • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
    • Human Rights Monitoring & Investigation
    • Women’s & Children’s Rights
    • Human Rights Education
    • Human Rights Film Festival
    • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Search
Ethiopian Human Rights Commission - EHRC
Powered by  GDPR Cookie Compliance
Privacy Overview

This website uses cookies so that we can provide you with the best user experience possible. Cookie information is stored in your browser and performs functions such as recognising you when you return to our website and helping our team to understand which sections of the website you find most interesting and useful.

Strictly Necessary Cookies

Strictly Necessary Cookie should be enabled at all times so that we can save your preferences for cookie settings.

If you disable this cookie, we will not be able to save your preferences. This means that every time you visit this website you will need to enable or disable cookies again.