Skip to content
Facebook XYouTube Linkedin Flicker Instagram WhatsApp Telegram
Ethiopian Human Rights Commission – EHRC
 
Ethiopian Human Rights Commission – EHRCEthiopian Human Rights Commission – EHRC

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተ.መ.ድ.) ሁሉን-አቀፍ የግምገማ መድረክ (Universal Periodic Review) ላይ የሲቪል ማኅበራት ሚና ማጎልበት

June 5, 2022October 6, 2022 Press Release

የምክረ ሃሳቦች አፈጻጸምን የመከታተልና ሪፖርት የማቅረብ ተቀዳሚ ኃላፊነት የመንግሥት ቢሆንም ሲቪል ማኅበራት ይህንን አስመልክቶ የራሳቸውን ምልከታ ሪፖርት ለማቅረብ ልዩ ዕድል አላቸው

Twitter Facebook Telegram Email Whatsapp Print

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ጋዜጣዊ መግለጫ
ግንቦት 28 ቀን 2014 ዓ.ም.

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን በግንቦት 25 ቀን 2014 ዓ.ም.  የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤት ሁሉን-አቀፍ የግምገማ መድረክ (Universal Periodic Review) ምክረ ሃሳቦች አፈጻጸምን ከማስተዋወቅና ከመቆጣጠር አንጻር የሲቪል ማኅበራት ያላቸውን ሚና የተመለከተ ሁለተኛ ዙር ስልጠና አዘጋጅቷል። 

ሁሉን-አቀፍ የግምገማ መድረክ (Universal Periodic Review – UPR) በመንግሥታት የሚመራ፣ አሳታፊና በፍላጎት/ትብብር ላይ የሚመሰረት ሂደት ሲሆን፣ ሁሉም የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አባል ሀገራት በሀገራቸው ያለውን የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ለማሻሻል እና የሰብአዊ መብቶች ግዴታቸውን ለመወጣት የወሰዱትን እርምጃዎች በማስመልከት ሪፖርት እንዲያቀርቡ ዕድል የሚሰጥ ነው። የግምገማውን ሂደት ተከትሎ በግምገማው የተለዩ ክፍተቶችንና ጉድለቶችን ለማሻሻል ምክረ ሃሳቦች ይሰጣሉ። ኢትዮጵያ በሦስት የ UPR ዙሮች (2002፣ 2006 እና 2011 ዓ.ም.) ባቀረበችው ሪፖርት ላይ አስተያየት ተቀብላለች። በ2011 ዓ.ም. በተደረገው ግምገማ ላይ ከ132 ሀገራት 327 ምክረ ሃሳቦች ለኢትዮጵያ የቀረቡ ሲሆን፣ ከነዚህ መካከል ኢትዮጵያ 270 ምክረ ሃሳቦችን ተቀብላ 57ቱን ሳትቀበል ቀርታለች። 

ከጥቅምት 17 እስከ 18 ቀን 2014 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽንና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ጽሕፈት ቤት (Office of the High Commissioner for Human Rights) የሁሉን-አቀፍ የግምገማ መድረክ (Universal Periodic Review) ምክረ ሃሳቦች፣ እንዲሁም የተ.መ.ድ. የሰብአዊ መብቶች ተቋማት የሚሰጡትን ምክረ ሃሳቦች አፈጻጸም ከመቆጣጠር አንጻር የሲቪል ማኅበራት ያላቸውን ሚና የተመለከተ ስልጠና አዘጋጅተው ነበር። የክትትል ስብሰባውም ይህንን ስልጠና ተከትሎ የተካሄደ ሲሆን፣ ዓላማው የሲቪል ማኅበራትን የሁሉን-አቀፍ የግምገማ መድረክ (Universal Periodic Review) ምክረ ሃሳቦች አፈጻጸም የመከታተል አቅምን የበለጠ ማሳደግ እና ለመከታተል የወሰዷቸውን እርምጃዎች ከሲቪል ማኅበራት ለመስማት ነበር።

የኢሰመኮ የሴቶችና ሕፃናት መብቶች ኮሚሽነር መስከረም ገስጥ በመክፈቻ ንግግራቸው “የምክረ ሃሳቦች አፈጻጸምን አስመልክቶ መንግሥት ሪፖርት የማቅረብ ተቀዳሚ ኃላፊነት ያለው ቢሆንም የሲቪል ማኅበራት የምክረ ሃሳቦቹን አፈጻጸም አስመልክቶ የራሳቸውን ምልከታ ሪፖርት ለማቅረብ ልዩ ዕድል አላቸው” ሲሉ አስረድተዋል። ኮሚሽነሯ አክለውም የሲቪል ማኅበራት እና ብሔራዊ የሰብአዊ መብቶች ተቋማት በሀገራቸው ስላለው የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ተዓማኒነት ያለው መረጃ በመስጠት በመንግሥት እና በአህጉራዊ እንዲሁም ዓለም አቀፋዊ የሰብአዊ መብቶች ተቋማት መካከል ያለውን ክፍተት ለመሙላት እንደሚያግዙ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ የሲቪል ማኅበራት በተባበሩት መንግሥታት ሁሉን-አቀፍ የግምገማ መድረክ (Universal Periodic Review) ላይ ካላቸው ተሳትፎ ጋር በተገናኘ፤ በ2011 ዓ.ም. በተካሄደው የሦስተኛው ዙር የግምገማ ወቅት፣ እነዚሁ ማኅበራት የተቀናጀ ጥረት በማድረግ ወደ 10 የሚሆኑ ሪፖርቶችን አቅርበው እንደነበር ተገልጿል። የሲቪል ማኅበራት ልዩ ልዩ ተግዳሮቶች ቢኖርባቸውም ተግዳሮቶችን በመቋቋምና ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የሲቪል ማኅበራት አዋጅ መሻሻልን ተከትሎ ለኢትዮጵያ የሲቪል ማኅበራት የተፈጠረውን የበለጠ ምቹ ሁኔታዎች በመጠቀም  ከሌሎች ዓለም አቀፍ እና አህጉራዊ የሰብአዊ መብቶች ተቋማት ጋር በመተባበር ጭምር አስተዋጾአቸውን ሊያጎለብቱ እንደሚገባም ተገልጿል፡፡ 

በተጨማሪም የኢትዮጵያ የሲቪል ማኅበራት በአሁኑ ወቅት አገልግሎት ላይ ያሉ የሁሉን-አቀፍ የግምገማ መድረክ (Universal Periodic Review) የመረጃ ቋቶችን በመጠቀም እንደ ኢሰመኮ፣ የተ.መ.ድ. የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ጽሕፈት ቤት (Office of the High Commissioner for Human Rights) እና የብሔራዊ የሰብአዊ መብቶች የድርጊት መርኃ ግብር ጽሕፈት ቤትን (National Human Rights Action Plan Office) ከመሰሉ እና ድጋፍ ሊሰጡ ከሚችሉ ተቋማት ጋር ተቀራርበው እንዲሰሩ ምክረ ሃሳብ ቀርቧል። በስብሰባው የሲቪል ማኅበራት የሁሉን-አቀፍ የግምገማ መድረክ (Universal Periodic Review) ምክረ ሃሳቦች አፈጻጸምን በተመለከተ ሪፖርት እንዲያቀርቡ የሚያስችል እንዲሁም ተጨባጭ ውጤቶች እና የጊዜ ሰሌዳዎችን የሚያካትት ረቂቅ-እቅድ ተነድፏል። 

የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ጽህፈት ቤት ዳይሬክተር አልባብ ተስፋዬ በመዝጊያ ንግግራቸው፣ “ኢሰመኮ የኢትዮጵያን የሲቪል ማኅበራት የተባበሩት መንግሥታት ሁሉን-አቀፍ የግምገማ መድረክን ምክረ ሃሳቦች አፈጻጸም ለመከታተል እንዲሁም ከዓለም አቀፍ እና አህጉራዊ የሰብአዊ መብቶች ተቋማት ጋር እንዲሰሩ ለማገዝ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ ይቀጥላል” ብለዋል።


Related posts

Signup for the Latest Update from EHRC

Submit your email to singup
Facebook Like us on FacebookXFollow us on XYouTube Follow us on YouTubeLinkedin Follow us on LinkedinWhatsApp WhatsAppTikTok TikTokTelegram TelegramInstagram InstagramFlicker Flickr

Useful Links

Get Involved

Connect with Us

Descriptive Text

We are an independent
national human rights
institution tasked with
the promotion and protection of human
rights in Ethiopia.

Submit your email to get the latest update from EHRC

Address: Sunshine Tower No. 5, Meskel Square, on Bole Road next to Hyatt Regency Hotel, Addis Ababa, Ethiopia Tel: +251115504031 | Fax: +251 11 550 4125 | PO Box 1165 Addis Ababa | Email: info@ehrc.org The contents of this website, excepting third party content for which the Commission bears no responsibility, may be freely used and copied for educational and other non-commercial purposes, provided that any such reproduction is accompanied by an acknowledgement of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC). Source of images used in the content of this website: EHRC Media and Communications Department Archive and Creative Common License. This website is managed by the Media and Communications team of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC).

Accessibility Adjustments

Powered by OneTap

How long do you want to hide the toolbar?
Hide Toolbar Duration
Select your accessibility profile
Vision Impaired Mode
Enhances website's visuals
Seizure Safe Profile
Clear flashes & reduces colour
ADHD Friendly Mode
Focused browsing, distraction-free
Blindness Mode
Reduces distractions, improves focus
Epilepsy Safe Mode
Dims colours and stops blinking
Content Modules
Font Size

Default

Line Height

Default

Colour Modules
Orientation Modules

We are using cookies to give you the best experience on our website.

You can find out more about which cookies we are using or switch them off in .

Scroll to top
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Search
Ethiopian Human Rights Commission - EHRC
Powered by  GDPR Cookie Compliance
Privacy Overview

This website uses cookies so that we can provide you with the best user experience possible. Cookie information is stored in your browser and performs functions such as recognising you when you return to our website and helping our team to understand which sections of the website you find most interesting and useful.

Strictly Necessary Cookies

Strictly Necessary Cookie should be enabled at all times so that we can save your preferences for cookie settings.