Skip to content
Facebook Twitter
  • አማርኛአማርኛ
  • EnglishEnglish
Ethiopian Human Rights Commission – EHRC
  • ስለ እኛ
    • ስለ ተቋማችን
    • ስለ ባልደረቦቻችን
    • ከእኛ ጋር ለመስራት
    • አግኙን
  • ክልሎች
        • ክልሎች

          ኢሰመኮ በኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት ማስከበርና መጠበቅ ኃላፊነት የተሰጠው ራሱን የቻለ የፌዴራል ተቋም ነው።

        • አዲስ አበባ
        • አፋር
        • አማራ
        • ቤኒሻንጉል-ጉሙዝ
        • ኦሮሚያ
        • ደቡብ ክልል
        • ሶማሌ
  • የስራ ዘርፎች
        • የስራ ዘርፎች

          እኛ በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶችን የማስፋፋት እና የማስጠበቅ ኃላፊነት የተሰጠን ገለልተኛ ብሔራዊ የሰብዓዊ መብቶች ተቋም ነን
        • የኢኮኖሚ፣ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ መብቶች
        • የሲቪልና ፖለቲካ መብቶች
        • የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች፣ የስደተኞችና ፍልሰተኞች መብቶች
        • የአካል ጉዳተኞች እና የአረጋዊያን መብቶች
        • የሰብአዊ መብቶች ትምህርት
        • የሰብአዊ መብቶች ክትትል እና ምርመራ
        • የሴቶች እና ሕጻናት መብቶች
  • ጋዜጣዊ መግለጫ
  • ሪፖርት
  • ሚዲያ
    • ኢሰመኮ በመገናኛ ብዙኃን
    • የኢሰመኮ ቪዲዮዎች
    • የኢሰመኮ ጽሑፎች
  • ተጨማሪ መረጃዎች
 
Ethiopian Human Rights Commission – EHRCEthiopian Human Rights Commission – EHRC

የአፍሪካን ቅድመ-ክስ ወይም ቅድመ ፍርድ እስራት ቀን ለማሰብ ኢሰመኮ እና አጋር ድርጅቶች በመተባበር ከወንጀል ፍትሕ አስተዳደር አካላት ከፍተኛ ተወካዮች ጋር የተደረገ ውይይት

April 29, 2022April 29, 2022 ጋዜጣዊ መግለጫ

የተራዘመ የቅድመ-ክስ እስራትን እና ተያያዥ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችን ለመከላከል የሁሉንም ፍትሕ አስተዳደር አካላት ቁርጠኛ ጥረት ይሻል

Twitter Facebook Telegram Email Whatsapp Print

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ጋዜጣዊ መግለጫ
ሚያዚያ 21 ቀን 2014 ዓ.ም.

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተ.መድ.) የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር የምሥራቅ አፍሪካ ጽሕፈት ቤት ጋር በመተባበር ሚያዝያ 20 ቀን 2014 ዓ.ም. “Africa Pre-trial Detention Day’’ ወይም “የአፍሪካን ቅድመ-ክስ/ቅድመ ፍርድ እስራት ቀን” አስመልክቶ የፌደራል እና የክልል ፍትሕ ተቋማትና መንግሥታዊ ያልሆኑ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት የውይይት መድረክ በአዲስ አበባ አካሂዷል፡፡ ይህ ቀን የአፍሪካ ሕብረት የሰብአዊ እና የሰዎች መብቶች ኮሚሽን እ.ኤ.አ. በኦክቶበር 15 ቀን 2015 ባሳለፈው ውሳኔ መሰረት በየዓመቱ ኤፕሪል 25 ቀን ታስቦ ይውላል።

በዝግጅቱ ላይ የቅድመ-ክስ እስራትን በተመለከተ ተፈጻሚ የሆኑ ዓለም አቀፍ፣ አህጉራዊ እና ብሔራዊ የሕግ ማዕቀፎችን በመዳሰስ በወንጀል ፍትሕ ሥርዓት ውስጥ የሚገኙ የቅድመ-ክስ እስረኞች አያያዝ እና ሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ተሳታፊዎች ሃሳብ ተለዋውጠዋል። ክፍተቶችን በመለየት ወደፊት በቅንጅት ሊሰሩ በሚችሏቸው ተግባራት ላይም መክረዋል።  የኢሰመኮ የክትትል እና ምርመራ ሥራ ክፍል በ2014 ዓ.ም. በጀት ዓመት ባከናወነው የማረሚያ ቤቶች ክትትል ያሉ ግኝቶችን ለተሳታፊዎች አቅርቧል፡፡

የኢሰመኮ የሲቪል፣ ፖለቲካ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ መብቶች ኮሚሽነር ዶ/ር አብዲ ጂብሪል በመክፈቻ ንግግራቸው፣ ክስ ሳይመሰረት የሚደረጉ እስሮች ለነጻነት መብት ጥሰት ዋነኛ ምክንያት መሆኑን ገልጸው፣ “በሕይወት የመኖር መብት፣ ከስቃይ እና ኢሰብአዊ አያያዝ የመጠበቅ መብት፣ የዋስትና መብት እና የተቀላጠፈ ዳኝነት የማግኘት መብትን የሚቃረን ነው” ብለዋል፡፡ 

በተለይም የተራዘመ የቅድመ-ክስ እስራት በራሱ የሰብአዊ መብት ጥሰት ሊሆን ስለሚችል የተራዘመ ከክስ በፊት ያለ እስራትን ለመከላከል ልዩ ትኩረት ይሻል፡፡ በሁሉም ባለድርሻ አካላት ዘንድ የተሻለ ተቋማዊ አሰራር እንዲኖር ለማድረግ የቅድመ-ክስ ወይም ፍርድ እስረኛ ሰዎች ጥበቃን በሚመለከት ያሉትን የሕግ ማዕቀፎች መፈተሽ፣ የአሰራር ክፍተቶችንና ተግዳሮቶችን መለየት እና አስፈላጊ ማሻሻያዎችን እና የእርምት እርምጃዎችን መውሰድ እንደሚኖርባቸው በውይይቱ ላይ ተገልጿል፡፡

ለውይይቱ በመነሻነት የቀረቡ ሌሎች ጽሑፎች ከወንጀል ጋር ተያይዞ በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋሉ ሴቶችን፣ሕፃናትን፣ ወጣት አጥፊዎችን አያያዝና በአጠቃላይ የቅድመ-ክስና ፍርድ እስርን ዳሰዋል። 

የተ.መ.ድ. የሰብአዊ መብቶች ጽ/ቤት የምሥራቅ አፍሪካ ቢሮ ተወካይ ማርሴል ክሌመንት አክፖቮ፣ “የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት የቅድመ-ክስ እስራትን በተመለከተ የጥበቃ እና ከለላ ድንጋጌዎችን ያካተተ ቢሆንም፣ በሀገሪቱ የዘፈቀደ እና የተራዘመ የቅድመ-ክስ እስራት አሳሳቢ ጉዳይ ነው” ብለዋል፡፡ አክለውም በመንግሥት በኩል የወንጀል ሥነ ሥርዓትና የማስረጃ ሕጉን ለማሻሻል እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።

የአፍሪካ ሕብረት ተወካይ ኡሳኒ ኒኮላስ በበኩላቸው ሁሉም ባለድርሻ አካላት የቅድመ-ክስ እስራትን በተመለከተ ኢትዮጵያ ያጸደቀቻቸውን ዓለም አቀፍ እና አህጉራዊ የሰብአዊ መብት ድንጋጌዎች እና በሕገ መንግሥቱ የተቀመጡ የመብት ጥበቃዎችን እንዲሁም የሉዋንዳ መመሪያዎችን በሙሉ ተፈጻሚነታቸው እውን መሆኑን ማረጋገጥ አለባቸው ብለዋል፡፡

የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዝደንት የተከበሩ ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ

የማጠቃለያ ሃሳብና የወደፊት አቅጣጫዎችን በተመለከተ ምክረ ሃሳቦች የሰጡት የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዝደንት የተከበሩ ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ “የቅድመ-ክስ እስራት ጥያቄን ተገቢነት በሚገባ በመመዘን እና የተጠርጣሪዎችን መብት በመጠበቅ በፍ/ቤቶች በኩል እያደገ የመጣ ለውጥ መኖሩን’’ አንስተው፤ ‘’ምንም እንኳን የአቅም ውስንነቶች ቢኖሩም መሰረታዊ ከሆነው መረጃ ልውውጥ ጀምሮ የቅንጅት ሥርዓት መዘርጋት እና ማጠናከር ተገቢ ነው” ብለዋል። በተጨማሪም በቅድመ-ክስና ፍርድ እስራት እንዲሁም በሌሎች እስራቶች ውስጥ የሴት እስረኞችን ልዩ ሁኔታ ማጤን ሌላኛው ትኩረት የሚሻ ጉዳይ መሆኑን አሳስበዋል፡፡

የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ በበኩላቸው የቅድመ-ክስ እስራት በሕግ በተመለከተው ሁኔታዎች ብቻ ማለትም ተጨማሪ የወንጀል ተግባርን ለመከላከል፣ የተጠርጣሪውን ማምለጥ ለመከላከል ወይም በወንጀል ፍትሕ አስተዳደር ውስጥ የተጠርጣሪዎችን ተገቢ ያልሆነ ጣልቃ ገብነት ለመከላከል በአሳማኝ ምክንያታዊ ሁኔታ ብቻ የሚፈቀድ በመሆኑ፤ የቅድመ ክስ እስርን ተገቢነትን ለመቆጣጠር የፍርድ ቤቶች ክትትል አስፈላጊ መሆኑን አስታውሰው፤ በፖሊስና ዐቃቤ ሕግ በኩልም ተገቢ ያልሆነ ቅድመ ክስ እስራትን ለማስቀረት የበኩላቸውን ኃላፊነት ሊወጡ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

Reports & Press Releases

December 10, 2021December 10, 2021 EHRC Quote
Join us and Stand Up for Human Rights on Human Rights Day
August 26, 2021February 20, 2022 ጋዜጣዊ መግለጫ
ምስራቅ ወለጋ፡ የነዋሪዎችን ደኅንነት ለማረጋገጥ የአካባቢው የፀጥታ ኃይል ሊጠናከር ይገባል
October 30, 2020May 21, 2021 ጋዜጣዊ መግለጫ
ስለ እስረኞች አያያዝ ክትትል
September 30, 2020May 12, 2021 ጋዜጣዊ መግለጫ
ኢሰመኮ በፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ህልፈት ሐዘኑን ይገልጻል

Signup for the Latest Update from EHRC

Submit your email to singup

Signup for the Latest Update from EHRC

    Submit your email here to get the latest update from EHRC.

    Facebook Like us on FacebookTwitter Follow us on Twitter

    ጠቃሚ ድረ-ገጾች

    • NANHRI
    • GANHRI
    • OHCHR
    • ACHPR

    ተሳተፉ

    • ከእኛ ጋር ለመስራት
    • አግኙን

    ከእኛ ጋር ይገናኙ

    • Facebook
    • Twitter
    • LinkedIn
    • YouTube
    EHRC
    እኛ ኢትዮጵያ ውስጥ የሰብአዊ መብቶችን የማስተዋወቅ እና
    የማስጠበቅ ኃላፊነት የተሰጠን ነፃ ብሄራዊ የሰብአዊ መብቶች
    ተቋም ነን
    Submit your email to get the latest update from EHRC

    © 2022 Copyright Ethiopian Human Rights Commission (EHRC). All Rights Reserved. Powered by 360Ground

    ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎት ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን።

    ኩኪዎችን መጠቀም ላይ መስማማትዎን እባክዎ ያሳውቁን።

    Scroll to top
    • የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ)
    • ስለ እኛ
      • ስለ ተቋማችን
      • ስለ ባልደረቦቻችን
      • ከእኛ ጋር ለመስራት
      • አግኙን
    • ክልሎች
      • አዲስ አበባ
      • አፋር
      • አማራ
      • ቤኒሻንጉል-ጉሙዝ
      • ሶማሌ
      • ደቡብ ክልል
      • ኦሮሚያ
    • የስራ ዘርፎች
      • የኢኮኖሚ፣ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ መብቶች
      • የሲቪልና ፖለቲካ መብቶች
      • የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች፣ የስደተኞችና ፍልሰተኞች መብቶች
      • የአካል ጉዳተኞች እና የአረጋዊያን መብቶች
      • የሴቶች እና ሕጻናት መብቶች
      • የሰብአዊ መብቶች ክትትል እና ምርመራ
      • የሰብአዊ መብቶች ትምህርት
    • ጋዜጣዊ መግለጫ
    • ሪፖርት
    • ሚዲያ
      • ኢሰመኮ በመገናኛ ብዙኃን
      • የኢሰመኮ ቪዲዮዎች
      • የኢሰመኮ ጽሑፎች
    • ተጨማሪ መረጃዎች
    • አማርኛአማርኛ
    • EnglishEnglish
    Facebook Twitter
    Search
    Powered by  GDPR Cookie Compliance
    Privacy Overview

    This website uses cookies so that we can provide you with the best user experience possible. Cookie information is stored in your browser and performs functions such as recognising you when you return to our website and helping our team to understand which sections of the website you find most interesting and useful.

    Strictly Necessary Cookies

    Strictly Necessary Cookie should be enabled at all times so that we can save your preferences for cookie settings.

    If you disable this cookie, we will not be able to save your preferences. This means that every time you visit this website you will need to enable or disable cookies again.