የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለ፣ በበዓሉ ላይ የተከሰቱትን ክስተቶች አስመልክተው በሰጡት ሀሳብ፣ የጸጥታ ኃይሎች በዓሉን ለማክበር በወጣው ሕዝብ ላይ ከልክ ያለፈ አላስፈላጊ ድብደባ፣ አስለቃሽ ጭስ፣ ጥይትና ሌሎች ከመጠን ያለፉ እምጃዎችን መውሰዳቸውን ጠቁመዋል
የኢሰመኮ የሕግና ፖሊሲ ሥራ ክፍል ዳይሬክተር ታሪኳ ጌታቸው ለአሜሪካ ድምጽ በሰጡት አስተያየት፣ “የፀጥታ ኃይሎች በወሰዱት ከልክ ያለፈ እርምጃ ቢያንስ የአንድ ሰው ህይወት ማለፉን አረጋግጠናል” ብለዋል
የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለ (ዶ/ር) በበዓሉ ላይ የተከሰቱትን ክስተቶች አስመልክተው በሰጡት ሀሳብ፣ የጸጥታ ኃይሎች በዓሉን ለማክበር በወጣው ሕዝብ ላይ ከልክ ያለፈ አላስፈላጊ ድብደባ፣ አስለቃሽ ጭስ፣ ጥይትና ሌሎች ከመጠን ያለፉ እምጃዎችን መውሰዳቸውን ጠቁመዋል
ሚሊዮን ዜጎቿ ተፈናቅለው የችግርና የሰቀቀን ኑሮ እየገፉ ቢሆንም የእነሱን ጉዳይ ጉዳዬ ብሎ የሚሰራ ተቋም የትኛው ነው ብላችሁ ብትፈልጉ አታገኙም
ከሰብአዊ መብቶች አኳያ ሊቀጥሉ እና ሊበረታቱ የሚገባቸው መልካም አሠራሮች ቢኖሩም የአረጋውያን መንከባከቢያ ማእከላቱ በአብዛኛው ቋሚ የገቢ ምንጭ የሌላቸው እና በገቢ ማስገኛ ሥራዎች ላይ ያላቸው ተሳትፎም ውስን መሆኑ አገልግሎታቸውን ለማስቀጠልና ዘላቂነቱን (sustainability) ለማረጋገጥ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑ በሪፖርቱ ተመላክቷል
በአፋር ክልል በጦርነት ምክንያት ለተደጋጋሚ መፈናቀል የተጋለጡ የሁለት ዞን ነዋሪዎች ለከፍተኛ የሰብአዊ ቀውስ መጋለጣቸው ተገለጠ። በተጨማሪም የንግድ እንቅስቃሴው ገደብ በመኖሩ ላልተገባ ኢኮኖሚያዊ ጫና መጋለጣቸውን እና በዘላቂነት እንዲቋቋሙ አለመደረጉን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ባደረገው ክትትል ማረጋገጡን አስታወቀ
ተጠያቂነትን ለማስፈን፣ እውነትን ለማውጣት፣ ማኅበረሰባዊ እርቅ እና ፈውስ ለማምጣት እንዲሁም የተጎጂዎችን መፍትሔ የማግኘት መብትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሁሉን አቀፍ ብሔራዊ የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ ተግባራዊ መደረግ አለበት
«ታጣቂዎቹ ጥቃቱን ባደረሱበት ከተማ ከማኅበረሰቡ ጋር ተቀላቅለው የሚኖሩ ተፈናቃዮችን ቤትለቤት እየዞሩ በተለይ የአማራ ብሔር ተወላጆችን ለይተው ገድለዋል» በማለት የምርመራ ግኝቱ ጠቁሟል
በወልቂጤ ከተማ ለውሃ አቅርቦት ጥያቄ አደባባይ በወጡ ነዋሪዎች ላይ ያልተመጣጠነ፤ ኃይል ተጠቅሞ ጥቃት በማድረስ ሕይወት እንዲጠፋና የአካል ጉዳት እንዲደርስ ያደረጉ የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ተጠያቂ እንዲሆኑ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አሳሰበ
ኮሚሽኑ ያወጣው የምርመራ ዘገባ እንደሚያሳየው ከተገደሉት ሰዎች መካከል 42ቱ በተፈናቃዮች የመጠለያ ጣቢያ ውስጥ እና ከተቀባይ ማኅበረሰብ ጋር ተቀላቅለው ይኖሩ የነበሩ ተፈናቃዮች እንዲሁም መንግሥትን ይደግፋሉ የተባሉ ነዋሪዎች ነበሩ