ኢሰመኮ ሰኔ ወር ላይ ባወጣው መግለጫ በሁለቱ ካምፖች የሚገኙት ነዋሪዎች የትግራይ ክልል አዋሳኝ ከሆኑ ከአባአላ፣ ከኮነባና ከበረሃሌ የተሰኙ ሦስት የአፋር ክልል ወረዳዎች የመጡ መሆናቸውን አስታውቆ ነበር
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን “ህገወጥና የዘፈቀደ እሥራት” ሲል በጠራው ሁኔታ አፋር ክልል ውስጥ ሰመራ አጋቲና ውስጥ ተይዘው የቆዩ የትግራይ ተወላጆች ተለቅቀው ወደ አብአላና ሌሎችም የቀድሞ መኖሪያ አካባቢዎቻቸው መመለስ መጀመራቸውን የክልሉ መንግሥት አስታወቀ
በአፋር ክልል ሰመራና አጋቲና ካምፖች ውስጥ ተይዘው የሚገኙ ሰዎች ያለ ቅድመ ሁኔታ በአስቸኳይ እንዲለቀቁ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ጠይቋል
በታኅሣሥ ወር 2014 ዓ.ም. ተይዘው የቆዩና በሁለቱ ካምፖች የሚገኙ ወደ 9,000 የሚጠጉ የትግራይ ተወላጆች ያሉበትን ሁኔታ በቦታው በመገኘት፣ በማነጋገር፣ የመንግሥት አካላትና አገልግሎት ሰጪዎችን እንዲሁም ሌሎች መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን በማነጋገር ክትትል ሲያደርግ መቆየቱን ገልጿል
ከየካቲት 17 እስክ 18 ቀን 2014 ዓ.ም. በአዲስ አባባ በተካሄደው ስብሰባ ከተሳተፉ መንግስታዊ ባለድርሻ አካላት ጋር የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችን መብቶች ለማስጠበቅ እና ለማስከበር የሚረዳ ተቋማዊ መዋቅሮች እና ቅንጅታዊ አሰራሮች ሊዘረጉ የሚቻልባቸው ምቹ ሁኔታዎችን ስለመፍጠር ውይይት ተደርጓል።
The Working Group is an experience sharing platform that brings together National Human Rights Institutions (NHRIs) in the Intergovernmental Authority for Development (IGAD) member states