በመፈናቀል ምክንያት ከትምህርት ገበታ ውጪ የሆኑ ሕፃናት የትምህርት አገልግሎት እንዲያገኙ እና ወደ መደበኛ የትምህርት ሥርዓት እንዲመለሱ የሁሉንም ጥረት ይፈልጋል
ሚሊዮን ዜጎቿ ተፈናቅለው የችግርና የሰቀቀን ኑሮ እየገፉ ቢሆንም የእነሱን ጉዳይ ጉዳዬ ብሎ የሚሰራ ተቋም የትኛው ነው ብላችሁ ብትፈልጉ አታገኙም
በአፋር ክልል በጦርነት ምክንያት ለተደጋጋሚ መፈናቀል የተጋለጡ የሁለት ዞን ነዋሪዎች ለከፍተኛ የሰብአዊ ቀውስ መጋለጣቸው ተገለጠ። በተጨማሪም የንግድ እንቅስቃሴው ገደብ በመኖሩ ላልተገባ ኢኮኖሚያዊ ጫና መጋለጣቸውን እና በዘላቂነት እንዲቋቋሙ አለመደረጉን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ባደረገው ክትትል ማረጋገጡን አስታወቀ
መንግሥት በአፋር ክልል በዞን ሁለት፣ በዞን አራት እንዲሁም በሰመራ ከተማ ለሚገኙ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች እና ተመላሾች በቂ፣ ወቅቱን የጠበቀ እና ተደራሽ የሆነ የሰብአዊ ድጋፍ የማቅረብ ኃላፊነቱን በተገቢው መንገድ መወጣት አለበት
«ታጣቂዎቹ ጥቃቱን ባደረሱበት ከተማ ከማኅበረሰቡ ጋር ተቀላቅለው የሚኖሩ ተፈናቃዮችን ቤትለቤት እየዞሩ በተለይ የአማራ ብሔር ተወላጆችን ለይተው ገድለዋል» በማለት የምርመራ ግኝቱ ጠቁሟል
ምንም እንኳን ለተፈናቃዮች ዘላቂ መፍትሔ ማፈላለግን በተመለከተ መንግሥት ተቀዳሚ ኃላፊነት ያለበት ቢሆንም የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብም የዘላቂ መፍትሔ ጥረቶች ስኬታማ እንዲሆኑ የማገዝ ኃላፊነት አለባቸው
መንግሥት የሲቪል ሰዎችን ደኅንነት ከማስጠበቅ በተጨማሪ ለግጭቱ ዘላቂ እና ሰላማዊ መፍትሔ ለማበጀት ተጨባጭ እርምጃ መውሰድ አለበት
በስደተኞች ሰብአዊ መብቶች ላይ ያለውን ግንዛቤ ማሳደግ፤ በመንግሥት እና በተራድኦ ተቋማት ለስደተኞች የሚቀርቡ የሰብአዊ ድጋፍ እና ሌሎች አገልግሎቶች አካታች፣ ተደራሽ እና ሰብአዊ ክብራቸውን የጠበቁ እንዲሆኑ ይረዳል
በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ጥበቃ እና ድጋፍ ዙሪያ የተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ የተፈናቃዮችን ዘላቂ መፍትሔ የማመቻቸት ሥራዎች በበቂ የሕግ ማዕቀፍ እንዲደገፍ ከማስቻል ረገድ ፋይዳው የጎላ ነው
ኢሰመኮ እንዳስታወቀዉ በየአካባቢዉ ስለሚፈናቀለዉ ሕዝብ በቂ መረጃ ባለመጠናቀሩ ለችግር ለተጋለጠዉ ተፈናቃይ የሰብዓዊ ድጋፎችን ለማቅረብ እንቅፋት ሆኗል