ለባለፉት በርካታ ወራት ሰፊ አካታች ሂደት ሲዘጋጅ የቆየው ይህ የስትራቴጂ እቅድ ኮሚሽኑ ለቀጣይ አምስት ዓመታት ሊሰሩና ትኩረት ሊሰጣቸው ይገባል ብሎ የለያቸው ቁልፍ የውጤት መስኮችንና ዋና ዋና ተግባራትን አካቷል።
Statement of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC) on the “Human Rights Situation in the Federal Democratic Republic of Ethiopia” delivered on the Occasion of the 69th Ordinary Session of the African Commission on Human and Peoples’ Rights – held between November 15 and December 5, 2021.
በአጠቃላይ ኮሚሽኑ ባደረገው ክትትል ለማረጋገጥ እንደቻለው ሰዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል ረገድ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መተግበር ባለበት መንገድ በተለይም “የጥብቅ አስፈላጊነት፣ ተመጣጣኝነት እና ከመድልዎ ነፃ መሆን” የሚሉትን የሰብአዊ መብት መርሆዎችን ባከበረ መልኩ አለመተግበሩን ተመልክቷል።
ኢሰመኮ በማቋቋሚያ አዋጁ በተሰጠው ሥልጣን መሰረት በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁም ወቅት ሰብአዊ መብቶችን የሚከታተል መሆኑንና የሚመለከታቸው አካላት በሙሉ ለኮሚሽኑ የክትትል ተግባራት ትብብር የማድረግ ግዴታ እንዳለባቸው ለማስታወስ ይወዳል
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ጽሕፈት ቤት፣ በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ትግራይ ክልል ውስጥ በተፈጠረው ግጭት ወቅት በሁሉም የግጭቱ ተሳታፊ አካላት ተፈጽመዋል የተባሉትን የዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች፣ የሰብአዊነት እና የስደተኞች ሕግጋት ጥሰቶች በተመለከተ በጋራ ያካሄዱት የምርመራ ሪፖርት የእንግሊዝኛውን ሪፖርት ያንብቡ  
Report covered period from 3 Nov 2020 to 28 June 2021; joint probe conducted from 16 May to 31 August 2021
ኢሰመኮ ከማረሚያ ቤቱ አስተዳደር ከፍተኛ ኃላፊዎች ጋር ባደረገው ውይይት የታሳሪዎችን ደህንነት ስለማረጋገጥ መወሰድ ባለባቸው እርምጃዎች ላይ ተመካክሯል
ጊዳ ኪራሙ ወረዳን ጨምሮ በተለያዩ የምስራቅ ወለጋ ወረዳዎች ውስጥ የሚገኙ ነዋሪዎች በአስጊ ሁኔታ ይገኛሉ
በተለይም በአሁኑ ወቅት ከሴዳል ወረዳ ወደ ሌሎች አካባቢዎች ሸሽተው የሚገኙ ነዋሪዎች እንደሚገልጹት፣ ከጥር ወር 2013 ዓ.ም. ጀምሮ በወረዳው በሚደርሱ ተደጋጋሚ ጥቃቶች ምክንያት በርካታ ነዋሪዎች የተፈናቀሉ ሲሆን፣ ከመጋቢት ወር 2013 ዓ.ም. ጀምሮ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ዝግ ሆነው ቆይተዋል።
ኢሰመኮ የፌዴራልና የክልሉ መንግስት የፀጥታ ኃይሎች በኪራሙ ወረዳ ላለው የፀጥታ ስጋት ዘላቂ መፍትሔ ለመስጠት እና በነዋሪዎች ላይ በተደጋጋሚ ጥቃት የሚያደርሱ ኃይሎችን ከሕግ ፊት ለማቅረብ ተጨባጭ እርምጃዎችን እንዲወስዱ ያሳስባል።