አባል ሀገራት ለአካል ጉዳተኞች የፖለቲካ መብቶችን እና በእነዚህ መብቶች ከሌሎች ጋር በእኩልነት የመጠቀም ዕድልን ያረጋግጣሉ። እንዲሁም የመምረጥና የመመረጥ መብትና ዕድልን ጨምሮ አካል ጉዳተኞች በቀጥታ ወይም በነጻነት በተመረጡ ተወካዮች አማካኝነት በፖለቲካና በሕዝባዊ ሕይወት ውስጥ ከሌሎች ጋር በእኩልነት ውጤታማ እና የተሟላ ተሳትፎ ማድረግ መቻላቸውን ያረጋግጣሉ
States Parties shall guarantee to persons with disabilities political rights and the opportunity to enjoy them on an equal basis with others, and shall undertake to ensure that persons with disabilities can effectively and fully participate in political and public life on an equal basis with others
መድረኩ የፖለቲካ ፓርቲዎችን መርኃ ግብሮች እና አሠራሮች አካታችነት ለመገምገም ዕድል ፈጥሯል
አረጋውያን በማንኛውም መጠለያ፣ መንከባከቢያ ወይም የድጋፍ ማእከል ውስጥ በሚኖሩበት ጊዜ ሰብአዊ መብቶቻቸው እና መሠረታዊ ነጻነቶቻቸው ሊረጋገጡላቸው ይገባል፤ይህም ስለሚደረግላቸው እንክብካቤ እና ስለሕይወታቸው ሁኔታ የመወሰን መብታቸውን እንዲሁም ክብራቸውን፣ እምነታቸውን፣ ፍላጎቶቻቸውን እና ግላዊ ሕይወታቸውን ሙሉ በሙሉ ማክበርን ይጨምራል።
Older Persons should be able to enjoy human rights and fundamental freedoms when residing in any shelter, care or treatment facility, including full respect for their dignity, beliefs, needs and privacy and for the right to make decisions about their care and quality of their lives
አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች ለሚያጋጥሟቸው ተግዳሮቶች የቴክኒክ እና ሙያ ስልጠና ተቋማት ተጨባጭ እርምጃዎችን ሊወስዱ ይገባል
ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የአካል ጉዳተኞች መብቶች ስምምነትን በአዋጅ ቁጥር 676/2002 ተቀብላ አጽድቃለች። ይህንን ስምምነት የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ኢትዮጵያ የተቀበለቻቸውን ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ሰነዶችን በሀገር ውስጥ ቋንቋዎች ለመተርጎምና ለማሰራጨት በአዋጅ ቁጥር 210/1992 (በአዋጅ ቁጥር 1224/2012 እንደተሻሻለው) አንቀጽ 6(8) በተሰጠው ስልጣን መሠረት ወደ አማርኛ ቋንቋ አስተርጉሞ አሳትሟል።
ኢትዮጵያ የአፍሪካ የሰዎችና ሕዝቦች መብቶች ቻርተር የአረጋውያን መብቶች ፕሮቶኮል በአዋጅ ቁጥር 1182/2012ተቀብላ አጽድቃለች። ይህንን ፕሮቶኮል የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ኢትዮጵያ የተቀበለቻቸውን ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ሰነዶችን በሀገር ውስጥ ቋንቋዎች ለመተርጎምና ለማሰራጨት በአዋጅ ቁጥር 210/1992 (በአዋጅ ቁጥር 1224/2012 እንደተሻሻለው) አንቀጽ 6(8) በተሰጠው ስልጣን መሠረት ወደ አማርኛ ቋንቋ አስተርጉሞ አሳትሟል።
This Executive Summary consolidates the key findings and issues of concern identified in the 4th Annual Ethiopia Human Rights Situation Report of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC), covering the fiscal year from June 2024 to June 2025 Click here for the Amharic version (በአማርኛ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ) Click here for the full report (Amharic)
ከሰኔ ወር 2016 ዓ.ም. እስከ ሰኔ ወር 2017 ዓ.ም. ያለውን ጊዜ የሚሸፍነውና ለአራተኛ በጀት ዓመት በዚህ መልኩ ተጠናቅሮ ይፋ የተደረገው ይህ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዓመታዊ ሪፖርት ኮሚሽኑ ባደራጃቸው ልዩ ልዩ የሥራ ክፍሎች እና የከተማ ጽሕፈት ቤቶች አማካኝነት በተሰበሰበ መረጃ መሠረት ሀገራዊ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታን ጠቅለል ባለ መልኩ የሚዳስስ ነው። የሪፖርቱ አንኳር ጉዳዮች Executive...