Skip to content
Facebook Twitter
Ethiopian Human Rights Commission – EHRC
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
        • Regions

          EHRC is an independent federal institution tasked with the promotion and protection of human rights in Ethiopia.

        • Addis Ababa
        • Afar
        • Amhara
        • Benishangul Gumuz
        • Gambella
        • Oromia
        • Somali
        • SNNP
        • Tigray
  • Areas of Work
        • Areas of Work

          We are an independent national human rights institution tasked with the promotion & protection of human rights in Ethiopia.

        • Economic, Social and Cultural Rights
        • Civil & Political Rights
        • IDPs, Refugees & Migrants Rights
        • Rights of Persons with Disabilities and the Rights of Older Persons
        • Women’s and Children’s Rights
        • HR Monitoring and Investigation
        • Human Rights Education
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • Events
  • Resources
 
Ethiopian Human Rights Commission – EHRCEthiopian Human Rights Commission – EHRC

በግል ሥራ እና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች ተቀጥረው የሚሠሩ ሠራተኞች የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ክትትል ሪፖርት የቀረቡ ምክረ ሃሳቦችን ተፈጻሚነት ለማረጋገጥ ኮሚሽኑ ቀጣይነት ያለው የውትወታ ሥራዎች ይሠራል

December 29, 2022December 29, 2022 Event Update

የሠራተኞች መብቶችን አፈጻጸም በበላይነት የማረጋገጥ ኃላፊነት የመንግሥት ቢሆንም ሌሎች የሚመለከታቸው አካላትም ኢሰመኮ በክትትል ሪፖርቱ ያቀረባቸውን ምክረ-ሃሳቦች ለመተግበር በጋራ መሥራት ይጠበቅባቸዋል

Twitter Facebook Telegram Email Whatsapp Download Print

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በግል ሥራ እና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲ ሠራተኞች ላይ የተሠሩ ጥናቶችን እና የቀረቡለትን በርካታ ቅሬታዎችን መሠረት በማድረግ በግል ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲ ሠራተኞች ሰብአዊ መብቶች አተገባበር ዙሪያ ያከናወነውን የክትትል ሥራ ሪፖርት ኅዳር 2 ቀን 2015 ዓ.ም. ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። በሪፖርቱ የተካተቱ ግኝቶች እና ምክረ ሃሳቦች አፈጻጸምን በተመለከተ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በአራት ከተሞች ማለትም በአዲስ አበባ፣ በባሕር ዳር፣ በሃዋሳ እና በጅማ  ተከታታይ የምክክር መድረኮች ተካሂደዋል። 

በመድረኮቹ ላይ ከፍርድ ቤቶች፣ አግባብነት ካላቸው የአስፈጻሚ አካላት፣ ከሠራተኛ ማኅበራት፣ ከአሠሪዎች፣ ከግል ሥራ እና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች፣ እንዲሁም ከሲቪል ማኅበራት የተውጣጡ አካላት ተሳትፈዋል።

በምክክር መድረኮቹ በሪፖርቱ የተለዩ የክትትል ግኝቶች እና የተሰጡ ምክረ-ሃሳቦች በኮሚሽኑ የሰብአዊ መብቶች ባለሞያዎች የቀረቡ ሲሆን በኢትዮጵያ የሠራተኞች ሰብአዊ መብቶችን የሚመለከቱ የሕግ ማዕቀፎችን የተመለከተ ገለጻ ለተሳታፊዎች ቀርቧል። የኤጀንሲ ሠራተኞች መብቶች በተለይም ምቹ የሥራ ሁኔታዎችን የማግኘት፣ እኩልነትና ከአድልዎ ነጻ የመሆን፣ የሥራ ዋስትና የማግኘት፣ ማኅበራዊ ዋስትና የማግኘት፣ የመደራጀት፣ ቅሬታ የማሰማት እንዲሁም ፍትሕ የማግኘት መብቶች እየተጣሱ እንደሆነ በመድረኮቹ ተነስቷል፡፡ እነዚህ ጉዳዮችን መሠረት በማድረግ ከሠራተኞች መብቶች ጋር በተገናኘ የሚስተዋሉ ችግሮችን እንዴት መቅረፍ ይቻላል፣ የክትትል ሪፖርቱ ከወጣ በኋላ ስለተወሰዱ እርምጃዎች እና በቀጣይም ከእያንዳንዱ ባለድርሻ አካላት ምን ይጠበቃል በሚሉ ጉዳዮች ላይ ከተሳታፊዎች ጋር ውይይት ተደርጓል። 

የኢሰመኮ የሲቪል እና ፖለቲካ፣ የማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መብቶች ኮሚሽነር ዶ/ር አብዲ ጅብሪል በመድረኮቹ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር፤ መድረኮቹ የተዘጋጁት በክትትል ሪፖርቱ የተገኙትን ግኝቶች እና የተሰጡትን ምክረ-ሃሳቦች በመተግበር የግል ሥራ እና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲ ሠራተኞች የሰብአዊ መብቶችን በተሻለ ሁኔታ ተግባራዊ እንዲሆኑ ለማስቻል ያለመ እንደሆነ ገልጸው፤ ሀገሪቱ የሠራተኞች የሰብአዊ መብቶችን በሚመለከት በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ሕገ-መንግሥት ውስጥ ከማካተትም በላይ ዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ፣ ማኅበራዊና ባህላዊ መብቶች ቃል ኪዳንን፣ አግባብነት ያላቸው የዓለም ሥራ ድርጅት ስምምነቶችን እና የተለያዩ የሠራተኞች መብቶችን የሚመለከቱ ዓለም አቀፍ ስምምነቶችን ተቀብላ ማጽደቋን አብራርተዋል። አክለውም መንግሥት እና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት በእነዚህ የሰብአዊ መብቶች የሕግ ማዕቀፎች ለተደነገጉት የሠራተኞች መብቶች መከበር እና መረጋገጥ እንዲሠሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡  

Location Addis Ababa

Reports & Press Releases

June 5, 2022October 6, 2022 Explainer
በመገናኛ ብዙኃን አማካኝነት ተፈጽሟል የሚባል ወንጀል እና ቅድመ ክስ እስር
November 10, 2022November 10, 2022 Event Update
National Human Rights Institutions (NHRIs) key to the ratification and implementation of regional integration mechanisms in Africa: The 5th NHRIs Forum and the 73rd Ordinary Session of the African Commission on Human and Peoples’ Rights (ACHPR)
March 24, 2022October 5, 2022 ኢሰመኮ በመገናኛ ብዙኃን
በከረዩ የሚችሌ ገዳ የጅላ አባላት ግድያ ላይ የተጀመረው የእርቅ ሂደት “ተጠያቂነትን ሊያደናቅፍ” እንደማይገባ ኢሰመኮ አሳሰበ – Ethiopia Insider
June 17, 2021July 14, 2021 EHRC Quote
IPC findings underscore dismal humanitarian situation in Tigray

Signup for the Latest Update from EHRC

Submit your email to singup
Facebook Like us on FacebookTwitter Follow us on Twitter

Useful Links

  • NANHRI
  • GANHRI
  • OHCHR
  • ACHPR

Get Involved

  • Jobs
  • Events
  • Contact Us
  • Telegram Bot

Connect with Us

  • Facebook
  • Twitter
  • LinkedIn
  • YouTube
EHRC
We are an independent national human rights
institution tasked with the promotion & protection of
human rights in Ethiopia
Submit your email to get the latest update from EHRC

Address: Sunshine Tower No. 5, Meskel Square, on Bole Road next to Hyatt Regency Hotel, Addis Ababa, Ethiopia
Tel: +251115504031 | Fax: +251 11 550 4125 | PO Box 1165 Addis Ababa | Email: info@ehrc.org

© 2023 Copyright Ethiopian Human Rights Commission (EHRC). All Rights Reserved. Powered by 360Ground

We are using cookies to give you the best experience on our website.

You can find out more about which cookies we are using or switch them off in settings.

Scroll to top
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
    • Addis Ababa
    • Afar
    • Amhara
    • Benishangul Gumuz
    • Gambella
    • Oromia
    • Somali
    • SNNP
    • Tigray
  • Areas of Work
    • Economic, Social and Cultural Rights
    • Civil & Political Rights
    • IDPs, Refugees & Migrants Rights
    • Rights of Persons with Disabilities and the Rights of Older Persons
    • Women’s and Children’s Rights
    • HR Monitoring and Investigation
    • Human Rights Education
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Videos
    • Newsletters
    • Events
  • Resources
Facebook Twitter
Search
Ethiopian Human Rights Commission - EHRC
Powered by  GDPR Cookie Compliance
Privacy Overview

This website uses cookies so that we can provide you with the best user experience possible. Cookie information is stored in your browser and performs functions such as recognising you when you return to our website and helping our team to understand which sections of the website you find most interesting and useful.

Strictly Necessary Cookies

Strictly Necessary Cookie should be enabled at all times so that we can save your preferences for cookie settings.

If you disable this cookie, we will not be able to save your preferences. This means that every time you visit this website you will need to enable or disable cookies again.