Skip to content
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Ethiopian Human Rights Commission – EHRC
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
        • Regions

          EHRC is an independent federal institution tasked with the promotion and protection of human rights in Ethiopia.

        • Addis Ababa
        • Afar
        • Amhara
        • Benishangul Gumuz
        • Gambella
        • Oromia
        • Somali
        • Tigray
        • Central Ethiopia
        • Dire Dawa
        • Harari
        • Sidama
        • South Ethiopia
        • South West Ethiopia Peoples'
  • Areas of Work
        • Areas of Work

          We are an independent national human rights institution tasked with the promotion & protection of human rights in Ethiopia.

        • Economic, Social & Cultural Rights
        • Civil & Political Rights
        • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
        • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
        • Women’s & Children’s Rights
        • Human Rights Education
        • Human Rights Monitoring & Investigation
        • Human Rights Film Festival
        • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
 
Ethiopian Human Rights Commission – EHRCEthiopian Human Rights Commission – EHRC

በ4ኛ ዙር የሁሉ-አቀፍ ግምገማ መድረክ (Universal Periodic Review – UPR) የተሰጡ ምክረ ሐሳቦች ላይ የተደረገ ምክክር

February 5, 2025February 5, 2025 Event Update

በሁሉ-አቀፍ ወቅታዊ የግምገማ መድረክ የተሰጡ ምክረ ሐሳቦችን ተቀብሎ መተግበር በኢትዮጵያ ያለው የሰብአዊ መብቶች ዐውድ ላይ አወንታዊ አስተዋጽዖ ያበረክታል

Twitter Facebook Telegram Email Whatsapp Print

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተ.መ.ድ.) የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤት (United Nations Human Rights Council – UNHRC) በጥር ወር 2017 ዓ.ም. በተካሄደው 4ኛው ዙር ሁሉ-አቀፍ ወቅታዊ የግምገማ መድረክ (Universal Periodic Review- UPR) ወቅት በኢትዮጵያ ያለውን የሰብአዊ መብቶች አያያዝ ለማሻሻል የተሰጡ ምክረ ሐሳቦችን ሀገር ውስጥ ካለው ነባራዊ ዐውድ ጋር በማዛመድ ሀገራዊ የሰብአዊ መብቶች አጀንዳ አድርጎ በጋራ ለመደገፍ ያለመ የምክክር መድረክ ጥር 20 እና 21 ቀን 2017 ዓ.ም. አካሄደ። በመድረኩ በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ የሚሠሩ የመንግሥት አካላት፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች፣ የጥናትና የምርምር ተቋማት፣ ሚዲያዎች እና ዩኒሴፍን ጨምሮ መንግሥታዊ ያልሆኑ ዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች ተሳትፈዋል።

የመድረኩ ተሳታፊዎች

ከዚህ ቀደም ከኅዳር 3 እስከ 6 ቀን 2017 ዓ.ም. በተ.መ.ድ. የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤት 47ኛው መደበኛ ስብሰባ ወቅት የኢትዮጵያ 4ኛው ዙር ሁሉ-አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ግምገማ በጄኔቫ፣ ስዊዘርላንድ መካሄዱ ይታወሳል። በዚህ ስብሰባ ኢትዮጵያ በ3ኛው ዙር የግምገማ መድረክ የተሰጧትን ምክረ ሐሳቦች ከመተግበር አንጻር እና የሰብአዊ መብቶች ሁኔታን በማሻሻል ረገድ በሀገር አቀፍ ደረጃ ያከናወነቻቸውን ተግባራት አስመልክቶ ሪፖርት አቅርባ በተ.መ.ድ. አባል ሀገራት የአቻ ለአቻ ግምገማ ሂደት አልፋለች። በዚህ ሂደት በኢትዮጵያ ያለውን የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ለማሻሻል መንግሥት ሊወስዳቸው የሚገቡ እርምጃዎችን በተለመከተ 114 የተ.መ.ድ. አባል ሀገራት 316 ምክረ ሐሳቦችን ሰጥተዋል። በዚህም መሠረት ከቀጣዩ 58ኛው የተ.መ.ድ. የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤት ስብሰባ አስቀድሞ ኢትዮጵያ ከእነዚህ 316 ምክረ ሐሳቦች ውስጥ የተቀበለቻቸውን ለይታ እንደምታሳውቅ ይጠበቃል፡፡

የመድረኩ ተሳታፊዎች

በምክክር መድረኩ የሁሉ-አቀፍ ወቅታዊ ግምገማ ሂደት ለሰብአዊ መብቶች መከበር እና መስፋፋት ያለውን ጉልህ ጠቀሜታ እንዲሁም በኢሰመኮ፣ በተለያዩ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች እና መንግሥታዊ ባልሆኑ ዓለም አቀፍ ተቋማት ቀርበው የነበሩ ሪፖርቶች ላይ ገለጻ ተሰጥቷል። ይህንንም ተከትሎ በሴቶች እና ሕፃናት፣ በሲቪል እና ፖለቲካዊ መብቶች፣ በማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መብቶች፣ በሽግግር ፍትሕና ተጠያቂነት እና የቀሩ ዓለም አቀፍ ስምምነቶችን ማጽደቅ ላይ ውይይት ተደርጓል። እንዲሁም እንደ ኢሰመኮ ያሉ ነጻ ተቋማትን ማጠናከር፣ በመንግሥት ተቋማት፣ በሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች እና በዓለም አቀፍ ድርጅቶች መካከል ያለውን ትብብር ማጠናከርን በተመለከተ የተሰጡ ምክረ ሐሳቦች በውይይቱ ተዳስሰዋል።

የመድረኩ ተሳታፊዎች

የመድረኩ ተሳታፊዎች የምክረ ሐሳቦቹ ተቀባይነት ማግኘት በመንግሥት እየተወሰዱ ያሉ መልካም እርምጃዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል እንዲሁም አሳሳቢ በሆኑ እና ትኩረት በሚሹ የሰብአዊ መብቶች ጉዳዮች ላይ የሕግ፣ የፖሊሲ እና የአሠራር ማሻሻያዎችን በማድረግ ተጨባጭ እርምጃዎች እንዲወሰዱ በማገዝ ሰብአዊ መብቶችን በኢትዮጵያ ለማስፋፋት እና ለማስከበር ጉልህ አስተዋጽዖ እንዳለው ገልጸዋል። በተጨማሪም ምክረ ሐሳቦቹን ከመቀበል ባለፈ በሚመለከታቸው የመንግሥት ተቋማት እቅዶች ውስጥ እንዲካተቱ ማድረግ፣ ተጨባጭ የሆኑ እርምጃዎች እንዲወሰዱ እና አፈጻጸማቸውን በተሟላ ሁኔታ መከታተል እንደሚያስፈልግ ተገልጿል።

የኢሰመኮ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ

የኢሰመኮ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ በ4ኛው ዙር የሁሉ-አቀፍ ወቅታዊ የግምገማ መድረክ የተሰጡ ምክረ ሐሳቦችን ተቀብሎ መተግበር በኢትዮጵያ ያለው የሰብአዊ መብቶች ዐውድ ላይ አወንታዊ አስተዋጽዖ እንደሚያበረክት ግምት ውስጥ በማስገባት መንግሥት በተቻለ መጠን አብዛኛዎቹን ምክረ ሐሳቦች እንዲቀበል በዕለቱ ጥሪ አቅርበዋል። ኢሰመኮ የኢትዮጵያ መንግሥት የሚቀበላቸውን ምክረ ሐሳቦች በመጪው ዓመታት ለመተግበር የሚከናወኑ ተግባራትን ለመደገፍ ከመንግሥት እና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር እንደሚሠራም ገልጸዋል።

Related posts

October 23, 2023October 27, 2023 Event Update
በብሔራዊ የንግድ እና ሰብአዊ መብቶች የድርጊት መርኃ ግብር ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር የተካሄደ ውይይት
December 25, 2024December 24, 2024 Event Update
በሰብአዊ መብቶች ተሟጋቾች ጥበቃ ላይ በማተኮር የተካሄደ ግልጽ የአቤቱታ መቀበያ መድረክ እና የባለድርሻዎች ውይይት
June 12, 2024June 12, 2024 Event Update
በወንጀል ነክ ነገር ውስጥ ገብተው በማቆያና ተሐድሶ ተቋም ውስጥ የሚገኙ ሕፃናት (ከ9 – 15 ዓመት) የሰብአዊ  መብቶች ሁኔታ ክትትል ግኝቶች ላይ የተካሄደ ውይይት
May 5, 2023May 5, 2023 Event Update
ሴቶችና ሕፃናት በወንጀል ፍትሕ ሥርዓቱ ውስጥ የሚያጋጥሟቸውን ተጨማሪ የመብቶች ጥሰት ለመከላከል ከፍትሕና ባለድርሻ አካላት ጋር የተደረገ ውይይት

Signup for the Latest Update from EHRC

Submit your email to singup
Facebook Like us on FacebookXFollow us on XYouTube Follow us on YouTubeLinkedin Follow us on LinkedinWhatsApp WhatsAppTikTok TikTokTelegram TelegramInstagram InstagramFlicker Flickr

Useful Links

  • NANHRI
  • GANHRI
  • OHCHR
  • ACHPR
  • TRANSITIONAL JUSTICE

Get Involved

  • Jobs
  • Events
  • Contact Us
  • Telegram Bot
  • Subscribe to our newsletter

Connect with Us

  • Facebook
  • Twitter
  • LinkedIn
  • YouTube
  • Flickr
  • Instagram
Descriptive Text

We are an independent
national human rights
institution tasked with
the promotion and protection of human
rights in Ethiopia.

Submit your email to get the latest update from EHRC

Address: Sunshine Tower No. 5, Meskel Square, on Bole Road next to Hyatt Regency Hotel, Addis Ababa, Ethiopia
Tel: +251115504031 | Fax: +251 11 550 4125 | PO Box 1165 Addis Ababa | Email: info@ehrc.org


The contents of this website, excepting third party content for which the Commission bears no responsibility,
may be freely used and copied for educational and other non-commercial purposes, provided that any such reproduction is accompanied by an acknowledgement of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC). Source of images used in the content of this website: EHRC Media and Communications Department Archive and Creative Common License.

This website is managed by the Media and Communications team of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC).

We are using cookies to give you the best experience on our website.

You can find out more about which cookies we are using or switch them off in .

Scroll to top
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
    • Addis Ababa
    • Afar
    • Amhara
    • Benishangul Gumuz
    • Central Ethiopia
    • Dire Dawa
    • Gambella
    • Harari
    • Oromia
    • Sidama
    • Somali
    • South Ethiopia
    • South West Ethiopia Peoples’
    • Tigray
  • Areas of Work
    • Economic, Social & Cultural Rights
    • Civil & Political Rights
    • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
    • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
    • Human Rights Monitoring & Investigation
    • Women’s & Children’s Rights
    • Human Rights Education
    • Human Rights Film Festival
    • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Search
Ethiopian Human Rights Commission - EHRC
Powered by  GDPR Cookie Compliance
Privacy Overview

This website uses cookies so that we can provide you with the best user experience possible. Cookie information is stored in your browser and performs functions such as recognising you when you return to our website and helping our team to understand which sections of the website you find most interesting and useful.

Strictly Necessary Cookies

Strictly Necessary Cookie should be enabled at all times so that we can save your preferences for cookie settings.

If you disable this cookie, we will not be able to save your preferences. This means that every time you visit this website you will need to enable or disable cookies again.