Skip to content
Facebook Twitter YouTube Linkedin Flicker
Ethiopian Human Rights Commission – EHRC
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
        • Regions

          EHRC is an independent federal institution tasked with the promotion and protection of human rights in Ethiopia.

        • Addis Ababa
        • Afar
        • Amhara
        • Benishangul Gumuz
        • Gambella
        • Oromia
        • Somali
        • SNNP
        • Tigray
  • Areas of Work
        • Areas of Work

          We are an independent national human rights institution tasked with the promotion & protection of human rights in Ethiopia.

        • Economic, Social & Cultural Rights
        • Civil & Political Rights
        • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
        • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
        • Human Rights Monitoring and Investigation
        • Women’s and Children’s Rights
        • Human Rights Education
        • Human Rights Film Festival
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • Events
  • Resources
 
Ethiopian Human Rights Commission – EHRCEthiopian Human Rights Commission – EHRC

የኢሰመኮ የኪነ-ጥበብና የሥነ ጥበብ አማካሪ ቡድን ለማቋቋም የሚረዳ ውይይት ተካሄደ

February 16, 2022August 28, 2023 Event Update, ስብሰባዎች እና ሌሎች ዝግጅቶች

ኮሚሽኑ ዓላማውን ለማስፈጸም ከሚሰራቸው ሰብአዊ መብቶችን የማስተማር እና የማስፋፋት ስራ ውጤታማ እንዲሆን ከተለያዩ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት ጋር በአጋርነት የሚሰራ ሲሆን፣ ከሀገራዊ የኪነጥበብና የሥነ ጥበብ ባለሞያዎችና ማኅበራት ጋር የሚያደርገውን ትብብር በተመሳሳይ መልኩ እኩል ክብደት የሚሰጠው ነው

Twitter Facebook Telegram Email Whatsapp Print

የካቲት 9 ቀን 2014 ዓ.ም. ደራሲያን፣ ፊልም ዳይሬክተሮች፣ የኪነጥበብና የሥነ ጥበብ ዘርፍ መምኅራን፣ የዜማና የግጥም ደራሲያን እንዲሁም የተለያዩ የኪነጥበብ ዝግጅቶች አስተባባሪዎችና የማኅበራት ተወካዮች የተገኙበትን እና በኢሰመኮ ዋና መስሪያ ቤት የተካሄደውን ይህን ስብሰባ ዓላማ ሲያስረዱ፣ የአጋርነት ስራ ክፍል ዳይሬክተር ሃና አንዳርጋቸው “በዋነኛነት የኪነጥበብ ቡድኑን አስፈላጊነት ማስተዋወቅና ባለሞያዎች ከኮሚሽኑ ጋር ለመስራት የሚያስችላቸውን ማዕቀፍ ለመዘርጋት የሚያስችል ግብዓት ለመቀበል” መሆኑን ገልጸዋል።  

የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ በበኩላቸው ኪነጥበብና ሥነ ጥበብ በባሕሪው ስለ መልካም ሥነ ምግባር እና ስለሰብአዊነት በማስተማር ረገድ የሚጫወተውን ሚና አስታውሰው፣ ኮሚሽኑም ይህንን ተገንዝቦ ሁሉንም የኪነጥበብ ዘርፎች ያካተተ የአማካሪ ቡድን ለማቋቋም እንደወሰነ አስረድተዋል። በተጨማሪም ኅዳር ወር 2014 ዓ.ም. በተመሳሳይ መልኩ ከበርካታ የኪነጥበብ ባለሞያዎች ጋር ባደረገው ውይይት ባለሞያዎቹ ኮሚሽኑን በበለጠ ሊያግዙ የሚችሉበት ይፋዊ ማዕቀፍ እንደሚያስፈልግ መወሰኑና፣ በታኅሣሥ ወር 2014 ዓ.ም. በኢሰመኮ አዘጋጅነት የተካሄደው የመጀመሪያው የሰብአዊ መብቶች ፊልም ፌስቲቫልም የዚህ ትብብር አንዱ ውጤት መሆኑ ተገልጿል።  

ይህ የመጀመሪያ ዙር ውይይት ኢሰመኮ ለዚሁ ዓላማ ያሰበውን የኪነ ጥበብ እና የሥነ ጥበብ አማካሪ ቡድን ኃላፊነትና ተግባራት የሚገልጽ ረቂቅ ቢጋር (Terms of Reference) ላይ ተወያይቷል። ስብሰባውን የተካፈሉት ባለሞያዎች ኮሚሽኑ ያለበትን ሀገራዊ ኃላፊነት ለመወጣት የኪነጥበብ እና የሥነ ጥበብ ባለሞያዎችን ለማሳተፍ ማቀዱ ተገቢና የሚመሰገን እንደሆነና በዚህ ውይይት የተጀመረውን ሂደት እንደሚደግፉት ገልጸው፣ በተዘጋጀው ረቂቅ ላይ በርካታ ገንቢ አስተያየቶች ሰጥተዋል።

Location Ethiopia

Related posts

February 25, 2022February 12, 2023 Event Update
የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችን አስመልክቶ የተለያዩ የመንግስት ተቋማት ሥልጣንና ኃላፊነት መለየት እና ቅንጅታዊ አሰራርን ማጠናከር
January 26, 2022August 28, 2023 Event Update
ኢሰመኮ በኦሮሚያ ክልል በተጠርጣሪዎች እና በታራሚዎች አያያዝ ላይ ከተለያዩ ተቋማት ከተውጣጡ አመራሮች ጋር ያደረገው ውይይት በተሳካ ሁኔታ ተጠናቀቀ
November 30, 2021October 3, 2023 1st film festival
ኢሰመኮ እና ኢሰመድህ በኅዳር እና በታኅሣሥ ወራት 2014 ዓ.ም. ታስበው የሚውሉ ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ቀናትን በተለያዩ ዝግጅቶች ያከብራሉ
December 10, 2021October 3, 2023 1st film festival
ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ቀን የሚያስቡ የተለያዩ ዝግጅቶች እና የመጀመሪያው የሰብአዊ መብቶች ፊልም ፌስቲቫል በተሳካ ሁኔታ ተጠናቀቁ

Signup for the Latest Update from EHRC

Submit your email to singup
Facebook Like us on FacebookTwitter Follow us on TwitterYouTube Follow us on YouTubeLinkedin Follow us on Linkedin

Useful Links

  • NANHRI
  • GANHRI
  • OHCHR
  • ACHPR

Get Involved

  • Jobs
  • Events
  • Contact Us
  • Telegram Bot
  • Subscribe to our newsletter

Connect with Us

  • Facebook
  • Twitter
  • LinkedIn
  • YouTube
  • Flickr
EHRC
We are an independent national human rights
institution tasked with the promotion & protection of
human rights in Ethiopia
Submit your email to get the latest update from EHRC

Address: Sunshine Tower No. 5, Meskel Square, on Bole Road next to Hyatt Regency Hotel, Addis Ababa, Ethiopia
Tel: +251115504031 | Fax: +251 11 550 4125 | PO Box 1165 Addis Ababa | Email: info@ehrc.org

© 2023 Copyright Ethiopian Human Rights Commission (EHRC). All Rights Reserved. Powered by 360Ground

We are using cookies to give you the best experience on our website.

You can find out more about which cookies we are using or switch them off in settings.

Scroll to top
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
    • Addis Ababa
    • Afar
    • Amhara
    • Benishangul Gumuz
    • Gambella
    • Oromia
    • Somali
    • SNNP
    • Tigray
  • Areas of Work
    • Economic, Social & Cultural Rights
    • Civil & Political Rights
    • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
    • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
    • Women’s & Children’s Rights
    • HR Monitoring & Investigation
    • Human Rights Education
    • Human Rights Film Festival
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Videos
    • Newsletters
    • Events
  • Resources
Facebook Twitter YouTube Linkedin Flicker
 

Loading Comments...
 

    Search
    Ethiopian Human Rights Commission - EHRC
    Powered by  GDPR Cookie Compliance
    Privacy Overview

    This website uses cookies so that we can provide you with the best user experience possible. Cookie information is stored in your browser and performs functions such as recognising you when you return to our website and helping our team to understand which sections of the website you find most interesting and useful.

    Strictly Necessary Cookies

    Strictly Necessary Cookie should be enabled at all times so that we can save your preferences for cookie settings.

    If you disable this cookie, we will not be able to save your preferences. This means that every time you visit this website you will need to enable or disable cookies again.