Skip to content
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Ethiopian Human Rights Commission – EHRC
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
        • Regions

          EHRC is an independent federal institution tasked with the promotion and protection of human rights in Ethiopia.

        • Addis Ababa
        • Afar
        • Amhara
        • Benishangul Gumuz
        • Gambella
        • Oromia
        • Somali
        • Tigray
        • Central Ethiopia
        • Dire Dawa
        • Harari
        • Sidama
        • South Ethiopia
        • South West Ethiopia Peoples'
  • Areas of Work
        • Areas of Work

          We are an independent national human rights institution tasked with the promotion & protection of human rights in Ethiopia.

        • Economic, Social & Cultural Rights
        • Civil & Political Rights
        • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
        • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
        • Women’s & Children’s Rights
        • Human Rights Education
        • Human Rights Monitoring & Investigation
        • Human Rights Film Festival
        • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
 
Ethiopian Human Rights Commission – EHRCEthiopian Human Rights Commission – EHRC

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የግል ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች እና ሰብአዊ መብቶች በኢትዮጵያ በሚል ርዕስ ዙሪያ የውይይት መድረክ አካሄደ

June 30, 2022October 6, 2022 Event Update

የኤጀንሲ ሠራተኞች መብቶች አተገባበርን በሚመለከት በኢሰመኮ የተደረገ የክትትል ሥራ የኤጀንሲ ሠራተኞች መብቶች ምቹ የሥራ ሁኔታዎችን የማግኘት፣ የእኩልነትና ከአድልዎ ነፃ የመሆን እንዲሁም የሥራ ዋስትና የማግኘት መብቶች እየተጣሱ እንደሆነ ማመላከቱ ተገልጾ በምክረ ሃሳቦች ላይ ከባለድርሻ አካላት ግብዓት ተሰብስቧል

Twitter Facebook Telegram Email Whatsapp Print

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ‘የግል ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች እና ሰብአዊ መብቶች በኢትዮጵያ’ በሚል ርዕስ ያዘጋጀው የምክክር መድረክ የሠራተኛ ማኅበራት አባላት፣ የተለያዩ የሲቪክ ማኅበራት ተወካዮች፣ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች የተውጣጡ ተሳታፊዎች እንዲሁም የግል ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች ተወካዮች በተገኙበት ባሳለፍነው አርብ ሰኔ 17 ቀን 2014 ዓ.ም. በአዲስ አበባ አዘጋጅቷል፡፡

የውይይት መድረኩ ላይ የኢሰመኮ የሲቪል፣ ፖለቲካዊ እና የማኅበራዊ-ኢኮኖሚያዊ መብቶች ኮሚሽነር ዶ/ር አብዲ ጅብሪል ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ሀገሪቱ የሠራተኞች መብቶችን በሚመለከት በሕገ-መንግሥቱ ካሉ ጉዳዩን ከሚመለከቱ ድንጋጌዎች በተጨማሪ የኢኮኖሚያዊ፣ የማኅበራዊና ባሕላዊ መብቶች ዓለም አቀፍ ቃልኪዳን፣ አግባብነት ያላቸው የዓለም ሥራ ድርጅት ስምምነቶችን እና የመሳሰሉ የተለያዩ የሠራተኞች መብቶችን የሚመለከቱ ዓለም አቀፍ ስምምነቶችን ተቀብላ ማፅደቋን በማብራራት ጀምረዋል። በመሆኑም “መንግሥት እና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት በእነዚህና መሰል ድንጋጌዎች ውስጥ ለተዘረዘሩ መብቶች መከበር መሥራት አለባቸው” ሲሉ ጠቁመዋል፡፡ ዶ/ር አብዲ አክለውም መድረኩ የተዘጋጀው ሀገሪቱ ውስጥ ያለውን የሠራተኞች የመብት ሁኔታ በምን መልኩ ለማሻሻል እንዲሁም አሁን ያሉ የመብቶች ጥሰቶችን በምን መልኩ ለማስቆም እንደሚቻል ግብዓት ለመሰብሰብ እና ለመመካከር እንደሆነ አስረድተዋል፡፡

በስብሰባው በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለውንና የኤጀንሲ ሠራተኞች መብቶችን በተመለከተ ያለውን የሕግ ማዕቀፍ የኮሚሽኑ የሰብአዊ መብቶች ባለሙያ ገልጻ ያደረጉ ሲሆን፣ ከዚህ ጋር በተያያዘ ተሳታፊዎች በሠራተኞች ላይ የሚስተዋለው ስለ ሕጎቹ እና ስለመብቶቻችው ያለው የመረጃ እና የፋይናንስ አቅም ማነስ የሕጎቹ አፈጻጸም ላይ እክል ሲፈጥር እንደሚታይ ጠቁመዋል፡፡

የኤጀንሲ ሠራተኞች መብቶች አተገባበርን በሚመለከት በኢሰመኮ የተደረገ የክትትል ሪፖርት ግኝቶች እና የተሰጡ ምክረ-ሃሳቦችም በምክክር መድረኩ ቀርበዋል፡፡ የክትትሉ ግኝቶች የኤጀንሲ ሠራተኞች መብቶች በተለይም ምቹ የሥራ ሁኔታዎችን የማግኘት፣ የእኩልነትና ከአድልዎ ነፃ የመሆን እንዲሁም የሥራ ዋስትና የማግኘት መብቶች እየተጣሱ እንደሆነ አመላክተዋል፡፡

እነዚህ ጉዳዮች ላይ በመመርኮዝ ተሳታፊዎች የቡድን ውይይት በማድረግ የሚስተዋሉ ችግሮችን እንዴት መቅረፍ እንደሚቻል፣ ከሚወክሏቸው ተቋማት በኩልም ችግሮቹን ከመቅረፍ አንጻር ምን እንደሚጠበቅ ያላቸውን አስተያየት ሰጥተዋል፡፡ በመጨረሻም የኢሰመኮ የኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ መብቶች ሥራ ክፍል ዳይሬክተር ዶ/ር ሚዛኔ አባተ ጉዳዩ ሁሉንም ባለድርሻዎች የሚመለከት መሆኑን በመግለጽ ውይይቱ ተገቢውን ግንዛቤ ከማስጨበጥ አንጻር መልካም ጅማሮ እንደሆነና ከባለድርሻ አካላቱ ጋር የሚኖረው ሥራ የሚቀጥል መሆኑን አመላክተዋል፡፡

Related posts

November 11, 2022November 11, 2022 Press Release
የሥራ እና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች አሠራር ሰብአዊ መብቶችን ሊያከብር ይገባል
December 29, 2022August 28, 2023 Event Update
በግል ሥራ እና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች ተቀጥረው የሚሠሩ ሠራተኞች የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ክትትል ሪፖርት የቀረቡ ምክረ ሃሳቦችን ተፈጻሚነት ለማረጋገጥ ኮሚሽኑ ቀጣይነት ያለው የውትወታ ሥራዎች ይሠራል
October 23, 2023October 27, 2023 Event Update
በብሔራዊ የንግድ እና ሰብአዊ መብቶች የድርጊት መርኃ ግብር ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር የተካሄደ ውይይት
July 11, 2023August 28, 2023 Event Update
በሲቪክ ማኅበራት፣ በመገናኛ ብዙኃን እና በኢሰመኮ መካከል ያለውን አጋርነት ማጠናከር

Signup for the Latest Update from EHRC

Submit your email to singup
Facebook Like us on FacebookXFollow us on XYouTube Follow us on YouTubeLinkedin Follow us on LinkedinWhatsApp WhatsAppTikTok TikTokTelegram TelegramInstagram InstagramFlicker Flickr

Useful Links

  • NANHRI
  • GANHRI
  • OHCHR
  • ACHPR
  • TRANSITIONAL JUSTICE

Get Involved

  • Jobs
  • Events
  • Contact Us
  • Telegram Bot
  • Subscribe to our newsletter

Connect with Us

  • Facebook
  • Twitter
  • LinkedIn
  • YouTube
  • Flickr
  • Instagram
Descriptive Text

We are an independent
national human rights
institution tasked with
the promotion and protection of human
rights in Ethiopia.

Submit your email to get the latest update from EHRC

Address: Sunshine Tower No. 5, Meskel Square, on Bole Road next to Hyatt Regency Hotel, Addis Ababa, Ethiopia
Tel: +251115504031 | Fax: +251 11 550 4125 | PO Box 1165 Addis Ababa | Email: info@ehrc.org


The contents of this website, excepting third party content for which the Commission bears no responsibility,
may be freely used and copied for educational and other non-commercial purposes, provided that any such reproduction is accompanied by an acknowledgement of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC). Source of images used in the content of this website: EHRC Media and Communications Department Archive and Creative Common License.

This website is managed by the Media and Communications team of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC).

We are using cookies to give you the best experience on our website.

You can find out more about which cookies we are using or switch them off in .

Scroll to top
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
    • Addis Ababa
    • Afar
    • Amhara
    • Benishangul Gumuz
    • Central Ethiopia
    • Dire Dawa
    • Gambella
    • Harari
    • Oromia
    • Sidama
    • Somali
    • South Ethiopia
    • South West Ethiopia Peoples’
    • Tigray
  • Areas of Work
    • Economic, Social & Cultural Rights
    • Civil & Political Rights
    • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
    • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
    • Human Rights Monitoring & Investigation
    • Women’s & Children’s Rights
    • Human Rights Education
    • Human Rights Film Festival
    • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Search
Ethiopian Human Rights Commission - EHRC
Powered by  GDPR Cookie Compliance
Privacy Overview

This website uses cookies so that we can provide you with the best user experience possible. Cookie information is stored in your browser and performs functions such as recognising you when you return to our website and helping our team to understand which sections of the website you find most interesting and useful.

Strictly Necessary Cookies

Strictly Necessary Cookie should be enabled at all times so that we can save your preferences for cookie settings.

If you disable this cookie, we will not be able to save your preferences. This means that every time you visit this website you will need to enable or disable cookies again.