Skip to content
Facebook XYouTube Linkedin Flicker Instagram WhatsApp Telegram
Ethiopian Human Rights Commission – EHRC
 
Ethiopian Human Rights Commission – EHRCEthiopian Human Rights Commission – EHRC

በአፋር ክልል የሰመራ ጣብያ ሙሉ በሙሉ መዘጋትን በተመለከተ

September 15, 2022October 7, 2022 EHRC Quote

በሰመራ ጣቢያዎች ተይዘው የነበሩ ሰዎች በኢሰመኮ ምክረ ሃሳቦች መሰረት እንዲለቀቁና በፍላጎታቸው መሰረት ወደመጡባቸው አካባቢዎች እንዲመለሱ መደረጉ ኢሰመኮ በበጎ የሚመለከተው ነው

Twitter Facebook Telegram Email Whatsapp Print

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ሰኔ 22 ቀን 2014 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ በሚገኙ ሰመራ እና አጋቲና ካምፖች በመባል በሚታወቁ ቦታዎች ከትግራይ ክልል አዋሳኝ ከሆኑ 3 የአፋር ክልል ወረዳዎች በታኅሣሥ ወር 2014 ዓ.ም. ተይዘው የቆዩና በሁለቱ ካምፖች የሚገኙ ወደ 9 ሺህ የሚጠጉ የትግራይ ተወላጆች ያሉበትን አሳሳቢ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ በመግለጽ በአፋጣኝና ያለቅድመ ሁኔታ እንደለቀቁ ማሳሰቡ ይታወሳል።

ኢሰመኮ በሁለቱ ካምፖች ተይዘው የሚገኙ ሰዎች ችግር በሚፈታበት ሁኔታ ላይ በሐምሌ 6 ቀን 2014 ዓ.ም. በሰመራ ከተማ ከክልሉ መንግሥት ኃላፊዎች ጋር በተደረገው ምክክር የክልሉ የመንግሥት ኃላፊዎች ችግሩን ለመፍታት አስፈላጊውን እርምጃ እንደሚወስዱ በገለጹት መሰረት በክልሉ ከሚንቀሳቀሱ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በመተባበር የምግብ፣ ሕክምና እና መጠለያ አቅርቦትን ለማሻሻል እንዲሁም የመንቀሳቀስ ነፃነቶቻቸውን በተሻለ ሁኔታ ለማረጋገጥ ጥረቶች ተደርገዋል፤ እንዲሁም ምዝገባ እና በሁለቱም ካምፖች የሚገኙ ሰዎች ወደየትኛው አካባቢዎች መመለስ እንደሚፈልጉ ለማወቅ የፍላጎት ዳሰሳዎች ተከናውናዋል። በማስከተልም ነሐሴ 12 ቀን 2014 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ በእነዚህ ካምፖች የሚገኙ የትግራይ ተወላጆችን ወደ መኖሪያ ቀዬአቸው የመመለሱን ሂደት በበጎ የሚመለከተው እና ክትትል ማድረጉን የሚቀጥል መሆኑን ማስታወቁ የሚታወስ ነው።

በዚህ መሰረት በሰመራ መጠለያ ጣቢያ ውስጥ የነበሩ ሰዎች በዋናነት በአፋር ክልል አብአላ አካባቢ ወደሚገኙ የቀድሞ መኖሪያ አካባቢዎቻቸው የመመለስ ፍላጎት በማሳየታቸው ከነሐሴ 17 ቀን 2014 ዓ.ም. እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2014 ዓ.ም. በተከናወነ የመመለስ ሥራ ወደ መኖሪያ አካባቢዎቻቸው እንዲመለሱ ተደርጎ የሰመራ መጠለያ ጣቢያ እንዲዘጋ ሆኗል።  

በአጋቲና የመጠለያ ካምፕ ውስጥ የሚገኙ ወደ 600 የሚጠጉ የትግራይ ተወላጆች በተከናወነው የፍላጎት ዳሰሳ ወደ ትግራይ ክልል መሄድ የሚፈልጉ መሆኑን የገለጹ ቢሆንም በአፋር ክልል መንግሥት እና በትግራይ ክልል አስተዳደር መካከል ቀጥተኛ ግንኙነት ባለመኖሩ በዓለም አቀፍ ድርጅቶች በኩል ለማስፈጸም ጥረቶች በመደረግ ላይ ባሉበት ወቅት ጦርነቱ በድጋሚ በመቀስቀሱ ለማስፈጸም አስቸጋሪ ሁኔታ መፈጠሩን ኮሚሽኑ ተገንዝቧል። የኢሰመኮ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ የአፋር ክልላዊ መንግሥት በሰመራ እና አጋቲና መጠለያ ጣቢያዎች ተይዘው የነበሩ ሰዎች በኢሰመኮ ምክረ ሃሳቦች መሰረት እንዲለቀቁና በፍላጎታቸው መሰረት ወደመጡባቸው አካባቢዎች እንዲመለሱ በማድረጉ ኢሰመኮ እውቅና የሚሰጥ መሆኑን ገልጸው በተለይ በዚህ ሥራ ላይ በዋናነት የተሳተፉትን የአፋር የክልል አደጋ መከላከል እና የምግብ ዋስትና ቢሮ፣ የክልሉ የጤና ቢሮ፣ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን እንዲሁም በዚህ ሂደት ለክልሉ መንግሥት ድጋፍ ያደረጉ ዓለም አቀፍ ተቋማትን ኮሚሽኑ ለማመስገን ይወዳል ብለዋል። 

Related posts

Signup for the Latest Update from EHRC

Submit your email to singup
Facebook Like us on FacebookXFollow us on XYouTube Follow us on YouTubeLinkedin Follow us on LinkedinWhatsApp WhatsAppTikTok TikTokTelegram TelegramInstagram InstagramFlicker Flickr

Useful Links

Get Involved

Connect with Us

Descriptive Text

We are an independent
national human rights
institution tasked with
the promotion and protection of human
rights in Ethiopia.

Submit your email to get the latest update from EHRC

Address: Sunshine Tower No. 5, Meskel Square, on Bole Road next to Hyatt Regency Hotel, Addis Ababa, Ethiopia Tel: +251115504031 | Fax: +251 11 550 4125 | PO Box 1165 Addis Ababa | Email: info@ehrc.org The contents of this website, excepting third party content for which the Commission bears no responsibility, may be freely used and copied for educational and other non-commercial purposes, provided that any such reproduction is accompanied by an acknowledgement of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC). Source of images used in the content of this website: EHRC Media and Communications Department Archive and Creative Common License. This website is managed by the Media and Communications team of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC).

Accessibility Adjustments

Powered by OneTap

How long do you want to hide the toolbar?
Hide Toolbar Duration
Select your accessibility profile
Vision Impaired Mode
Enhances website's visuals
Seizure Safe Profile
Clear flashes & reduces colour
ADHD Friendly Mode
Focused browsing, distraction-free
Blindness Mode
Reduces distractions, improves focus
Epilepsy Safe Mode
Dims colours and stops blinking
Content Modules
Font Size

Default

Line Height

Default

Colour Modules
Orientation Modules

We are using cookies to give you the best experience on our website.

You can find out more about which cookies we are using or switch them off in .

Scroll to top
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Search
Ethiopian Human Rights Commission - EHRC
Powered by  GDPR Cookie Compliance
Privacy Overview

This website uses cookies so that we can provide you with the best user experience possible. Cookie information is stored in your browser and performs functions such as recognising you when you return to our website and helping our team to understand which sections of the website you find most interesting and useful.

Strictly Necessary Cookies

Strictly Necessary Cookie should be enabled at all times so that we can save your preferences for cookie settings.