Skip to content
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Ethiopian Human Rights Commission – EHRC
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
        • Regions

          EHRC is an independent federal institution tasked with the promotion and protection of human rights in Ethiopia.

        • Addis Ababa
        • Afar
        • Amhara
        • Benishangul Gumuz
        • Gambella
        • Oromia
        • Somali
        • Tigray
        • Central Ethiopia
        • Dire Dawa
        • Harari
        • Sidama
        • South Ethiopia
        • South West Ethiopia Peoples'
  • Areas of Work
        • Areas of Work

          We are an independent national human rights institution tasked with the promotion & protection of human rights in Ethiopia.

        • Economic, Social & Cultural Rights
        • Civil & Political Rights
        • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
        • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
        • Women’s & Children’s Rights
        • Human Rights Education
        • Human Rights Monitoring & Investigation
        • Human Rights Film Festival
        • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
 
Ethiopian Human Rights Commission – EHRCEthiopian Human Rights Commission – EHRC

የግል ሥራ እና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲ ሠራተኞችን መብቶች አተገባበር አስመልክቶ ኢሰመኮ በክትትል ሪፖርቱ ያቀረባቸው ምክረ ሐሳቦች የተፈጻሚነት ሁኔታ

May 29, 2024May 29, 2024 Press Release, Report

የግል ሥራ እና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲ ሠራተኞችን የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ለማሻሻል ፈጣን የሕግ ማዕቀፍ ማሻሻያ እርምጃ ያስፈልጋል

Twitter Facebook Telegram Email Whatsapp Download Download Print

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በኅዳር ወር 2015 ዓ.ም. ይፋ ባደረገው የግል ሥራ እና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲ ሠራተኞች መብቶች አተገባበር የክትትል ሪፖርት ላይ ያቀረባቸውን ምክረ ሐሳቦች ተፈጻሚነት አስመልክቶ ከመስከረም 6 እስከ 12 ቀን 2016 ዓ.ም. የትግበራ ክትትል በማከናወን ያዘጋጀውን ባለ 12 ገጽ ሪፖርት ዛሬ ይፋ አድርጓል፡፡

ኢሰመኮ በዚህ የትግበራ ክትትል በዋናው የክትትል ሪፖርት የተጠቆሙ ምክረ ሐሳቦች ያሉበትን የአተገባበር ሁኔታ ለመገምገም እንዲሁም ከክትትሉ በኋላ የተፈጠሩ ክፍተቶች ለመለየት ገላጭ የክትትል ዘዴን (qualitative follow-up methodology) ተጠቅሟል። በአዲስ አበባ፣ በሃዋሳ እና ጅማ ከተሞች ከሚገኙ የኤጀንሲ ሠራተኞች፣ የግል ሥራ እና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች፣ ተጠቃሚ ድርጅቶች፣ ከሚመለከታቸው የመንግሥት ተቋማት እና ሌሎች ባላድርሻ አካላት በአጠቃላይ ከ57 ተሳታፊዎች ጋር በተደረጉ ቃለ መጠይቆች፣ በአካል ምልከታ እና በሰነዶች ትንተና መረጃዎች እና ማስረጃዎችን አሰባስቧል።

ኢሰመኮ በኅዳር ወር 2015 ዓ.ም. ይፋ ባደረገው ዋናው የክትትል ሪፖርት በግል ሥራ እና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች ተቀጥረው የሚሠሩ ሠራተኞች መብቶች በተለይም ምቹ የሥራ ሁኔታዎችን የማግኘት፣ የእኩልነትና ከአድልዎ ነጻ የመሆን፣ የሥራ ዋስትና የማግኘት፣ ማኅበራዊ ዋስትና የማግኘት፣ የመደራጀት፣ ቅሬታ የማሰማት እንዲሁም ፍትሕ የማግኘት መብቶች አተገባበር ላይ ከፍተኛ ክፍተቶች የሚስተዋሉ መሆኑን አመላክቷል። ለእነዚህም ክፍተቶች አስተዋጽዖ ያደረጉትን ምክንያቶች የለየ ሲሆን፣ በተለይም የኤጀንሲ ሠራተኞችን በተመለከተ ተፈጻሚነት ያለው ዋና የሕግ ማዕቀፍ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 በግል ሥራና እና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች በኩል ቀጥሮ ማሠራትን ዕውቅና ቢሰጥም የሁለትዮሽ የሥራ ግንኙነትን ብቻ ከግምት ውስጥ በማስገባት የተቀረጸ ነው። በመሆኑም የሦስትዮሽ የሥራ ግንኙነትን ሙሉ በሙሉ በሚሸፍን እና በዚህ ዐይነት የሥራ ግንኙነት ውስጥ የሚሳተፉትን አካላት ኃላፊነቶች እና የመንግሥትን ግዴታዎች በአግባቡ በሚደነግግ መልኩ እንዲሻሻል ወይም ለዚሁ ዓላማ ራሱን የቻለ አዲስ ሕግ እንዲወጣ ምክረ ሐሳብ አቅርቧል። ኢሰመኮ በዋናው የክትትል ሪፖርት ከሕግ ማዕቀፍ ጋር ከተያያዙ ምክረ ሐሳቦች ባሻገር ሌሎች ከትግበራ፣ ከቁጥጥርና ክትትል እንዲሁም ከግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራ ጋር የተገናኙ ዝርዝር የመፍትሔ ሐሳቦችንም ሰጥቷል።

የትግበራ ክትትል ሪፖርቱ በዋናው የክትትል ሪፖርት የተሰጡትን ምክረ ሐሳቦች ተከትሎ በመንግሥት የቁጥጥር እና ክትትል አካላት እንዲሁም በአንዳንድ ተጠቃሚ ድርጅቶች እና የግል ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች በኩል የሠራተኞችን መብቶች ሊያስጠብቁ የሚችሉ የተወሰኑ አወንታዊ እርምጃዎች ቢወሰዱም አብዛኛዎቹ ምክረ ሐሳቦች እየተተገበሩ አለመሆናቸውን ያመለክታል። በተለይም በዋናው የክትትል ሪፖርት በተመለከተው መሠረት የሕግ ማሻሻያ እርምጃዎች አለመወሰዳቸው፣ የኤጀንሲ ሠራተኞችን መብቶች፣ ደኅንነት እና ጥቅማጥቅም ለማስጠበቅ ጠቀሜታ ያለው የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መመሪያ ቁጥር 45/2013 ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ አለመደረጉ፣ እንዲሁም የኤጀንሲ ሠራተኞች የሥራ ዋስትና ማጣት ሪፖርቱ ካመላከታቸው ዋና ዋና አሳሳቢ ጉዳዮች መካከል ናቸው። ለምሳሌ ከ3000 በላይ የሚሆኑ የአንድ ኤጀንሲ ሠራተኞች የሥራ መቋረጥ ሥጋት ያለባቸው መሆኑ ተጠቃሽ ነው።

ኢሰመኮ የትግበራ ክትትሉን ግኝቶች መሠረት በማድረግ መንግሥት፣ ተጠቃሚ ድርጅቶች እና ኤጀንሲዎች በዋናው የክትትል ሪፖርት የተካተቱትን ሁሉንም ምክረ ሐሳቦች በአግባቡ ተግባራዊ እንዲያደርጉ፤ በተለይም የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጁ የሦስትዮሽ የሥራ ግንኙነቶችን ሙሉ በሙሉ በሚሸፍን እና በዚህ ዐይነት የሥራ ግንኙነት ውስጥ የሚሳተፉትን  አካላት ኃላፊነቶች እና የመንግሥትን ግዴታዎች በግልጽ በሚያስቀምጥ መልኩ እንዲሻሻል ወይም ለዘርፉ ራሱን የቻለ የሕግ ማዕቀፍ እንዲፈጠር ምክረ ሐሳብ አቅርቧል። ይህ እርምጃ ተግባራዊ እስኪሆን ድረስም የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የኤጀንሲ ሠራተኞችን የሥራ ውል በሚሰማሩበት ሥራ ቀጣይነት ላይ የተመሠረተ እንዲሆን ለማድረግ የሚያስችል መመሪያ እንዲያወጣ መክሯል።

የኢሰመኮ የማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መብቶች ሥራ ክፍል ዳይሬክተር ዶ/ር ብራይትማን ገብረ ሚካኤል ኢሰመኮ የምርመራና ክትትል ሥራዎቹን ተመርኩዞ የሚያቀርባቸውን ምክረ ሐሳቦች በአግባቡ መተግበር በኢትዮጵያ የተሻለ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ለመፍጠር አስፈላጊ መሆኑን አስታውሰው፣ “የግል ሥራ እና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲ ሠራተኞችን መብት አተገባበር ለማሻሻል መንግሥትን፣ ተጠቃሚ ድርጅቶችን እና ኤጀንሲዎችን ጨምሮ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በትብብር መሥራት ይገባቸዋል። በተለይም ከሕግ ማዕቀፍ ማሻሻያ ጋር በተያያዘ የተነሱት ምክረ ሐሳቦች ፈጣን ምላሽ የሚፈልጉ ናቸው” ብለዋል።

ሙሉ ሪፖርቱን እዚህ ያንብቡ

Related posts

November 11, 2022November 11, 2022 Press Release
የሥራ እና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች አሠራር ሰብአዊ መብቶችን ሊያከብር ይገባል
December 29, 2022August 28, 2023 Event Update
በግል ሥራ እና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች ተቀጥረው የሚሠሩ ሠራተኞች የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ክትትል ሪፖርት የቀረቡ ምክረ ሃሳቦችን ተፈጻሚነት ለማረጋገጥ ኮሚሽኑ ቀጣይነት ያለው የውትወታ ሥራዎች ይሠራል
June 30, 2022October 6, 2022 Event Update
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የግል ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች እና ሰብአዊ መብቶች በኢትዮጵያ በሚል ርዕስ ዙሪያ የውይይት መድረክ አካሄደ
May 8, 2023June 11, 2024 Press Release
ኮሚሽኑ የሚያቀርባቸው ምክረ ሐሳቦች በመንግሥት አስፈጻሚ አካላት ተግባራዊነታቸው እንዲረጋገጥ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ልዩ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል

Signup for the Latest Update from EHRC

Submit your email to singup
Facebook Like us on FacebookXFollow us on XYouTube Follow us on YouTubeLinkedin Follow us on LinkedinWhatsApp WhatsAppTikTok TikTokTelegram TelegramInstagram InstagramFlicker Flickr

Useful Links

  • NANHRI
  • GANHRI
  • OHCHR
  • ACHPR
  • TRANSITIONAL JUSTICE

Get Involved

  • Jobs
  • Events
  • Contact Us
  • Telegram Bot
  • Subscribe to our newsletter

Connect with Us

  • Facebook
  • Twitter
  • LinkedIn
  • YouTube
  • Flickr
  • Instagram
Descriptive Text

We are an independent
national human rights
institution tasked with
the promotion and protection of human
rights in Ethiopia.

Submit your email to get the latest update from EHRC

Address: Sunshine Tower No. 5, Meskel Square, on Bole Road next to Hyatt Regency Hotel, Addis Ababa, Ethiopia
Tel: +251115504031 | Fax: +251 11 550 4125 | PO Box 1165 Addis Ababa | Email: info@ehrc.org


The contents of this website, excepting third party content for which the Commission bears no responsibility,
may be freely used and copied for educational and other non-commercial purposes, provided that any such reproduction is accompanied by an acknowledgement of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC). Source of images used in the content of this website: EHRC Media and Communications Department Archive and Creative Common License.

This website is managed by the Media and Communications team of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC).

We are using cookies to give you the best experience on our website.

You can find out more about which cookies we are using or switch them off in .

Scroll to top
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
    • Addis Ababa
    • Afar
    • Amhara
    • Benishangul Gumuz
    • Central Ethiopia
    • Dire Dawa
    • Gambella
    • Harari
    • Oromia
    • Sidama
    • Somali
    • South Ethiopia
    • South West Ethiopia Peoples’
    • Tigray
  • Areas of Work
    • Economic, Social & Cultural Rights
    • Civil & Political Rights
    • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
    • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
    • Human Rights Monitoring & Investigation
    • Women’s & Children’s Rights
    • Human Rights Education
    • Human Rights Film Festival
    • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Search
Ethiopian Human Rights Commission - EHRC
Powered by  GDPR Cookie Compliance
Privacy Overview

This website uses cookies so that we can provide you with the best user experience possible. Cookie information is stored in your browser and performs functions such as recognising you when you return to our website and helping our team to understand which sections of the website you find most interesting and useful.

Strictly Necessary Cookies

Strictly Necessary Cookie should be enabled at all times so that we can save your preferences for cookie settings.

If you disable this cookie, we will not be able to save your preferences. This means that every time you visit this website you will need to enable or disable cookies again.