የንግድ ተግባራት በአግባቡ ካልተመሩ የጤና፣ የመኖሪያ ቤት፣ የምግብ፣ ውሃ፣ ማኅበራዊ ደኅንነት፣ የመሥራት መብት፣ ደኅንነቱ የተጠበቀ የሥራ ሁኔታ የማግኘት እንዲሁም የንግድ ማኅበራትን የመመሥረትና የመቀላቀል መብቶች አተገባበር ላይ ተጽዕኖ ይፈጥራሉ
ሰዎች በሰላም ወጥቶ የመግባት፣ ከቦታ ቦታ በነጻነት የመንቀሳቀስ እና የመሥራት መብቶቻቸው እንዲከበሩና መልካም እመርታዎች ዘላቂነት እንዲኖራቸው የትጥቅ ግጭቶችን ግልጽ እና አካታች በሆነ ሂደት ማስቆም፣ በቁርጠኝነት የሕግ የበላይነትን ማስከበር ይገባል
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በተለይ በአፍሪካ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚታሰበውን እና በየዓመቱ እ.ኤ.አ. ሰኔ 30 የሚውለውን የአፍሪካ ሳይንሳዊ ሕዳሴ ቀን (Africa Scientific Renaissance)፣ እንዲሁም የዓመቱ የትምህርት ወቅት መዝጊያን በማስመልከት በተዘጋጀ ማብራሪያ ትምህርት መሠረታዊ የሰብአዊ መብት መሆኑን በማስታወስ፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ በግጭት፣ በመፈናቀል፣ በአካል ጉዳት፣ በመሠረተ ልማት ውድመት፣ እንዲሁም በኑሮ ውድነት እና ሌሎች ምክንያቶች ከትምህርት ውጪ ሆነው ለበርካታ ወራት የቆዩ ሕፃናትን በ2016 ዓ.ም. ወደ ትምህርት እንዲመለሱ የማድረጉ ሥራ ከፍተኛ እና የተቀናጀ ትኩረት እንዲሰጠው ጥሪ ያቀርባል።
የማሰቃየት ተግባር ምን ተጽዕኖዎችን ያስከትላል? የማሰቃየትን ተግባርን የሚከለክሉ ዓለም አቀፍ ስምምነቶች የትኞቹ ናቸው? የማሰቃየት ተግባራትን የሚከለክሉ የኢትዮጵያ ሕጎች የትኞቹ ናቸው?
አረጋውያን እነማን ናቸው? በአረጋውያን ላይ የሚደርስ ጥቃት ምን ማለት ነው? አረጋውያን ላይ የሚደርሱ የጥቃት አይነቶች ምን ምን ናቸው?
ደኅንነቱ እና ጤንነቱ የተጠበቀ የሥራ ሁኔታ መብት ሲባል ምን ማለት ነው? ደኅንነቱ እና ጤንነቱ የተጠበቀ የሥራ ሁኔታ መብት ጋር የተገናኙ ግዴታዎች ምንድን ናቸው?
በቅርቡ ይፋ በተደረገው ‘‘የኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ የፖሊሲ አቅጣጫ አማራጮች’’ ሰነድ ዙሪያ በሚደረጉ ምክክሮችም ሆነ በሌሎች የሽግግር ፍትሕ ሂደቶች የአረጋውያን እና አካል ጉዳተኞችን ተሳትፎ እና ተካታችነት ለማረጋገጥ አስፈላጊ የሆኑ እርምጃዎችን መውሰድ ይገባል
ኤፕለፕሲ ያለባቸው ሰዎችና ቤተሰቦቻቸው ለከፍተኛ መገለልና መድሎ የተጋለጡ መሆናቸውን ከግምት በማስገባት፤ ስለሕመሙ ያሉ የተሳሳቱ አመለካከቶች ላይ ግንዛቤ ለመፍጠርና መብቶቻቸውን ለማስከበር ሲባል በዓለም አቀፍ ደረጃ የካቲት ወር ሁለተኛው ሰኞ ዓለም አቀፍ የኤፕለፕሲ ቀን ሆኖ ይታወሳል
ቅድመ ማስለቀቅ፣ በማስለቀቅ ወቅት እንዲሁም ድኅረ ማስለቀቅ ጊዜ መንግሥት ሊያሟላ የሚገባቸው የሰብአዊ መብቶች መርሆችን ያልተከተለ ሲሆን በኃይል ማፈናቀል እንደተፈጸመ ይቆጠራል፡፡ ይዞታ የማስለቀቅ ተግባር በአጠቃላይ ሰዎችን ቤት አልባ እንዲሆኑ እና ለሌሎች የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ተጋላጭ ማድረግ የለበትም
ይህ የኢሰመኮ ገላጭ ጽሑፍ ሴሬብራል ፓልዚ ላይ ግንዛቤን ለመፍጠር ይረዳል