ኮሚሽኑ ከመደበኛው የክትትል እና የምርመራ ሥራው ጎን ለጎን ጉዳዩ የሚመለከታቸውን ባለድርሻ አካላት በሙሉ በማነጋገር እና በመመካከር ሰብአዊ መብቶች እንዲከበሩና እንዲረጋገጡ የሚያስችል የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችን የመከላከል ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል
በጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም. የተካሄደው ይህ ሕዝበ ውሳኔ ኮሚሽኑ ክትትል ባደረገባቸው 186 ጣቢያዎች ከታዩ መለስተኛ የምርጫ አስተዳደር ግድፈቶች (minor electoral irregularities) ውጪ፤ አጠቃላይ ምርጫው ሰላማዊ፣ ሥርዓታዊ እና ከጎሉ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች ነጻ የነበረ ነው
ከዚህ ቀደም በተካሄዱ ምርጫዎች የተስተዋሉ በጎ ጅማሮች እንዲቀጥሉና ኮሚሽኑ ለእርምት እና ለማስተካከያ ያቀራባቸው ምክረ ሃሳቦች እንዲተገበሩ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ግዴታቸውን ሊወጡ ይገባል
ስምምነቱ የሰብአዊ መብቶች እሴቶችን ወደ ማኅበረሰቡ ከማስረጽ አኳያ ተደራሽነትን በመጨመር በኢትዮጵያ ዘላቂና ውጤታማ በሆነ መንገድ የሰብአዊ መብቶች ባህልን ለማስፈን ከፍተኛ አስተዋፅዖ አለው
በየዓመቱ የሚከበረውን ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ቀንን ለማሰብ በኢሰመኮ አዘጋጅነት የተጀመረው የሰብአዊ መብቶች ፊልም ፌስቲቫል፤ በቀጣይ ዓመት በተመሳሳይ ወቅት ለሦስተኛ ዙር የሚመለስ ይሆናል
ሕዝባዊ የአቤቱታ መቀበያ መድረክ ግልጽ እና ሕዝባዊ ተሳትፎ የሚደረግበትና መብቶቻቸው የተጣሱ ተጎጂዎች፣ ምስክሮች፣ ሌሎች ባለድርሻ አካላት እንዲሁም የሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት በተገኙበት የሚከናወን የምርመራ ስልት ነው
ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ቀንን ለማሰብ እና የሰብአዊ መብቶች ግንዛቤ ለማዳበር ሰፊ ተደራሽነት ያለውን የፊልም ጥበብን በመጠቀም በሰብአዊ መብቶች ጉዳይ ላይ የሚያጠነጥኑ ፊልሞች ለእይታ እና ለውይይት ይቀርባሉ
በክልሉ በሲቪል ሰዎች ላይ እየደረሰ ያለው ግድያ፣ አካል ጉዳት እና መፈናቀል መጠነ ሰፊ ምርመራን ጨምሮ እየደረሰ ካለው ከፍተኛ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ጋር የሚመጣጠን የፌዴራል መንግሥቱን አፋጣኝ እርምጃ እና ተጨባጭ ዘላቂ መፍትሔ የሚሻ ነው
የተሟላ አዲስ የሕግ ማዕቀፍ እንዲወጣ ወይም የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ እንዲሻሻል ያስፈልጋል
መንግሥት በኮንሶ ዞን እና በአጎራባች ልዩ ወረዳዎች ለሚገኙ ተፈናቃዮች የተደራጀ የምዝገባ ሥርዓት ማከናወን፣ የወሳኝ ኩነት አገልግሎትን ጨምሮ ሌሎች ሰነዶችን ማግኘት እንዲችሉ ማድረግ፣ እንዲሁም በክልሉ ለተደጋጋሚ መፈናቀል መንስዔ ለሆኑ ጉዳዮች ዘላቂ መፍትሔ ሊያፈላልግ ይገባል