ከግጭቶቹ ጋር በተያያዘ ከቀያቸው ለተፈናቀሉ ነዋሪዎች በቂ የሆነ አስቸኳይ የሰብአዊ ድጋፍ በአፋጣኝ ማቅረብን ጨምሮ፣ ተፈናቃዮች እና ነዋሪዎች ወደ ዘላቂ ሰላም የሚመለሱበት ሁኔታ ተግባራዊ ሊደረግ ይገባል
በተጎጂዎች ፍላጎት እና ቅድሚያ በሚሰጧቸው ጉዳዮች ላይ ጠንካራ ትኩረት በማድረግ፣ ያለፉ ጥሰቶችን በሚመጥን መልኩ ምላሽ ለመስጠት፣ ፍትሐዊና ሰላማዊ የወደፊት ነገን ለመመሥረት፣ እንዲሁም ሀገራዊ አንድነትን ለማጎልበት፣ እውነተኛ፣ ሁሉን አቀፍና የተሟላ የሽግግር ፍትሕ ሂደት ተግባራዊ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን የሪፖርቱ ግኝቶች አጉልተው ያሳያሉ
Findings highlight the necessity of implementing a genuine, inclusive, and comprehensive transitional justice process, with a strong focus on the needs and priorities of victims, to confront past violations, establish a just and peaceful future, and foster national cohesion
በሀገር ውስጥ በሴቶች እና በሕፃናት የመነገድ ድርጊትን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር ሁሉን አቀፍ ሕጋዊ፣ ፖለቲካዊ፣ አስተዳደራዊ እና ማኅበራዊ ስልቶች ሊነደፉ ይገባል
በወልቂጤ ከተማ ጥቅምት 2 ቀን 2016 ዓ.ም. ለተከሰተው ሁከት እና የደረሰውን ጉዳት በተመለከተ ተገቢውን ማጣራት በማድረግ ተጠያቂነት ማረጋገጥ፣ እንዲሁም ለተፈናቃዮች እና ተጎጂዎች አስፈላጊው ድጋፍ እና ካሳ ሊሰጣቸው ይገባል
በኢትዮጵያ የስደተኞች እና ጥገኝነት ጠያቂዎች ሰብአዊ መብቶች አጠባበቅ ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ለማረም ትኩረት ሰጥቶ መሥራት ያስፈልጋል
የፍትሕ አካላት ሰብአዊ መብቶችን ለማክበር እና ለማስከበር ቁርጠኛ እንዲሁም በኮሚሽኑ ክትትል የተለዩ ግኝቶችንና የተሰጡ ምክረ ሐሳቦችን በቅንነት ተቀብሎ መፈጸም ይጠበቅባቸዋል
CSOs, EHRC, and human rights defenders should seize this unique opportunity by actively contributing to the transitional justice process and ably representing the interests of victims and affected communities
በአዲስ መልኩ በሚዋቀሩ አካባቢዎች የሚነሱ የደመወዝ እና ተያያዥ ጥያቄዎች አፋጣኝ መፍትሔ መስጠት በጤና እና በትምህርት መብት እንዲሁም በአካባቢዎቹ አጠቃላይ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ላይ ያሉ ሥጋቶችን ይቀርፋል
የጥላቻ ንግግርን ለመቆጣጠር የሚወሰዱ እርምጃዎች ሐሳብን በነጻነት የመግለጽ መብትን የማያጣብቡ መሆናቸውን ማረጋገጥ ያስፈልጋል