የመተከል ዞን ሰላም እና ደኅንነት ዘላቂ በሆነ መልኩ እንዲመለስ የተጀመሩ የሰላም ሂደቶችን አፈጻጸምና ውጤት መከታተል ይገባል
ሰዎች በሰላም ወጥቶ የመግባት፣ ከቦታ ቦታ በነጻነት የመንቀሳቀስ እና የመሥራት መብቶቻቸው እንዲከበሩና መልካም እመርታዎች ዘላቂነት እንዲኖራቸው የትጥቅ ግጭቶችን ግልጽ እና አካታች በሆነ ሂደት ማስቆም፣ በቁርጠኝነት የሕግ የበላይነትን ማስከበር ይገባል
ለሰብአዊ መብቶች ጥሰት የሥር መንስኤ የሆኑ የተጠያቂነት አለመኖር፣ የሕግ የበላይነት መላላት እና የሰላም እና ደኅንነት እጦት ዘላቂ መፍትሔ ለማስገኘት የመንግሥት ከፍተኛ እና ያልተቋረጠ ጥረት ያሻል (የ2015 በጀት ዓመት የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ሪፖርት)
ስልጠናዎቹ በአካል ጉዳተኞች፣ በሕፃናት፣ እንዲሁም በሕግ ታራሚዎች ሰብአዊ መብቶች ላይ ያተኮሩ ናቸው
የሦስትዮሽ ትብብሩ የመብት ተሟጋቾች ሊደርስባቸው የሚችለውን ጫና እና እንግልት በጋራ ለመከላከል እና ለመቋቋም ትልቅ ሚና ይኖረዋል
የፍትሕ አካላትን የበጀት ውስንነት በመቅረፍ የሚሰጧቸውን አገልግሎቶች ለአካል ጉዳተኞች እና ለአረጋውያን ተደራሽ ለማድረግ የባለድርሻ አካላት በቂ ትኩረት ይፈልጋል
በሥራ ዘርፉ የሚንቀሳቀሱ አስፈጻሚ ተቋማትን በማጠናከር፣ ባለድርሻዎችን አቀናጅቶ እና አስተባብሮ የሚመራ ሥርዓት መዘርጋት አለበት
በማረሚያ ቤቶች እና በፖሊስ ጣቢያዎች የታራሚዎችን እና የተጠርጣሪዎችን አያያዝ ለማሻሻል በኮሚሽኑ የሚሰጡ ምክረ ሐሳቦችን በቁርጠኝነት መፈጸም ያስፈልጋል
National Human Rights Institutions should continue to challenge and advise governments on legal reforms and monitor the implementation of their recommendations
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በተለይ በአፍሪካ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚታሰበውን እና በየዓመቱ እ.ኤ.አ. ሰኔ 30 የሚውለውን የአፍሪካ ሳይንሳዊ ሕዳሴ ቀን (Africa Scientific Renaissance)፣ እንዲሁም የዓመቱ የትምህርት ወቅት መዝጊያን በማስመልከት በተዘጋጀ ማብራሪያ ትምህርት መሠረታዊ የሰብአዊ መብት መሆኑን በማስታወስ፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ በግጭት፣ በመፈናቀል፣ በአካል ጉዳት፣ በመሠረተ ልማት ውድመት፣ እንዲሁም በኑሮ ውድነት እና ሌሎች ምክንያቶች ከትምህርት ውጪ ሆነው ለበርካታ ወራት የቆዩ ሕፃናትን በ2016 ዓ.ም. ወደ ትምህርት እንዲመለሱ የማድረጉ ሥራ ከፍተኛ እና የተቀናጀ ትኩረት እንዲሰጠው ጥሪ ያቀርባል።