አዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮችን ጨምሮ በሁሉም ክልሎች በሚካሄደው የፎቶግራፍ እና የአጫጭር ፊልሞች ውድድር ክህሎት እና ዝንባሌ ያላቸው ሰዎች እና ተቋማት በሙሉ እንዲሳተፉ ተጋብዘዋል
ስልጠናዎቹ በሽግግር ፍትሕ፣ በታራሚዎች እና በተጠርጣሪዎች ሰብአዊ መብቶች አያያዝ ላይ ያተኮሩ ናቸው
መንግሥት በተለያዩ ቦታዎች የተፈጸሙ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች ላይ የተሟላ ማጣራት በማድረግ ተጠያቂነትን ሊያረጋግጥ እንዲሁም በድርጊቶቹ ተጎጂ ለሆኑ ሰዎች ፍትሕ ሊያሰፍን ይገባል
አባል ሀገራት አረጋውያን ሴቶች ከጥቃት፣ ከወሲባዊ ጥቃት እንዲሁም በጾታ ላይ ከተመሠረተ መድልዎ መጠበቃቸውን ማረጋገጥ አለባቸው
ተመጣጣኝ ማመቻቸት በአካል ጉዳተኝነት ዐውድ ውስጥ ወዲያውኑ ተፈጻሚ ሊሆን የሚገባው አድሏዊ ልዩነት ያለማድረግ ግዴታ አካል ነው
Reasonable accommodation is an intrinsic part of the immediately applicable duty of non-discrimination in the context of disability
ሕፃናት ምቹ እና ሰብአዊ መብቶቻቸውን ያከበረ ትምህርት እንዲያገኙ ባለድርሻ አካላት ተገቢውን ትኩረት ሊሰጡ ይገባል
ማንኛውም ሰው በነጻነት የመሰለውን አመለካከት የመያዝ እና ሐሳቡን የመግለጽ መብት አለው፤ ይህ መብት ያለጣልቃ ገብነት አመለካከት የመያዝ እና በሀገራት ድንበር ሳይወሰኑ በማናቸውም ዐይነት የመገናኛ ዘዴዎች መረጃዎችና ሐሳቦችን የማፈላለግ፣ የመቀበል እና የማሰራጨት ነጻነትን ይጨምራል
ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የአካል ጉዳተኞች መብቶች ስምምነትን በአዋጅ ቁጥር 676/2002 ተቀብላ አጽድቃለች። ይህንን ስምምነት የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ኢትዮጵያ የተቀበለቻቸውን ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ሰነዶችን በሀገር ውስጥ ቋንቋዎች ለመተርጎምና ለማሰራጨት በአዋጅ ቁጥር 210/1992 (በአዋጅ ቁጥር 1224/2012 እንደተሻሻለው) አንቀጽ 6(8) በተሰጠው ስልጣን መሠረት ወደ አማርኛ ቋንቋ አስተርጉሞ አሳትሟል።
ኢትዮጵያ የአፍሪካ የሰዎችና ሕዝቦች መብቶች ቻርተር የአረጋውያን መብቶች ፕሮቶኮል በአዋጅ ቁጥር 1182/2012ተቀብላ አጽድቃለች። ይህንን ፕሮቶኮል የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ኢትዮጵያ የተቀበለቻቸውን ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ሰነዶችን በሀገር ውስጥ ቋንቋዎች ለመተርጎምና ለማሰራጨት በአዋጅ ቁጥር 210/1992 (በአዋጅ ቁጥር 1224/2012 እንደተሻሻለው) አንቀጽ 6(8) በተሰጠው ስልጣን መሠረት ወደ አማርኛ ቋንቋ አስተርጉሞ አሳትሟል።