የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ/ኮሚሽኑ) በሕግ ከተሰጡት ሥልጣን፣ ተግባርና ኃላፊነቶች መካከል የሰብአዊ መብቶች ክትትል ማድረግ አንዱ በመሆኑ በተለይ ለሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች ተጋላጭ የሆኑ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ታሳቢ ያደረጉ የክትትል ሥራዎችን ያከናውናል፡፡ አረጋውያን ከዕድሜ መግፋት ጋር ተያይዘው ለሚመጡ አድሎዎች እና ለሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች ተጋላጭ በመሆናቸው እና የሚያስፈልጋቸውን ድጋፍ ለመስጠት ሲባል አረጋውያንን በአንድ ማእከል ውስጥ አሰባስቦ እንክብካቤ መስጠት...
ስምምነቱ “የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲው የሲቪክ ማኅበራትን ጨምሮ ከሁሉም ባለድርሻ አካላት በሕዝባዊ ምክክር የሚገኙ ግብአቶችን መሠረት አድርጎ እና መደበኛ ሀገራዊ የፖሊሲ አወጣጥ ሂደቶችን ተከትሎ ሊዘጋጅ እንደሚገባ” ያስቀምጣል
ምንም እንኳን ለተፈናቃዮች ዘላቂ መፍትሔ ማፈላለግን በተመለከተ መንግሥት ተቀዳሚ ኃላፊነት ያለበት ቢሆንም የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብም የዘላቂ መፍትሔ ጥረቶች ስኬታማ እንዲሆኑ የማገዝ ኃላፊነት አለባቸው
በኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ከተከሰተው ችግር ጋር በተያያዘ ግድያዎች፣ እስሮች፣ መዋከቦች እና እንግልቶች መፈጸማቸውን ኢሰመኮ ባለፈው ሳምንት ባወጣው መግለጫ ማስታወቁ ይታወሳል
አባል ሀገራት አረጋውያን በሁሉም ጊዜ ሰብአዊ እንክብካቤ፣ ጥበቃ እና ክብር እንዲያገኙ የማድረግ እና የሚያስፈልጋቸውን የሕክምና ድጋፍ እና እንክብካቤ እንዳይነፈጋቸው የማድረግ ግዴታ አለባቸው
States Parties shall ensure that older persons receive humane treatment, protection and respect at all times and are not left without needed medical assistance and care
ኤፕለፕሲ ያለባቸው ሰዎችና ቤተሰቦቻቸው ለከፍተኛ መገለልና መድሎ የተጋለጡ መሆናቸውን ከግምት በማስገባት፤ ስለሕመሙ ያሉ የተሳሳቱ አመለካከቶች ላይ ግንዛቤ ለመፍጠርና መብቶቻቸውን ለማስከበር ሲባል በዓለም አቀፍ ደረጃ የካቲት ወር ሁለተኛው ሰኞ ዓለም አቀፍ የኤፕለፕሲ ቀን ሆኖ ይታወሳል
The state-linked Ethiopian Human Rights Commission has also stepped into the fray, releasing a statement on Friday accusing the security forces of using excessive force against followers of the main church
ከሰሞኑ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ከተከሰተው ችግር ጋር በተያያዘ የመንግሥት የፀጥታ አባላት ተመጣጣኝ ባልሆነ ኃይል በጥይት እና በድብደባ ግድያዎችን መፈጸማቸውን ኢሰመኮ አስታወቀ
ኮሚሽኑ ከመደበኛው የክትትል እና የምርመራ ሥራው ጎን ለጎን ጉዳዩ የሚመለከታቸውን ባለድርሻ አካላት በሙሉ በማነጋገር እና በመመካከር ሰብአዊ መብቶች እንዲከበሩና እንዲረጋገጡ የሚያስችል የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችን የመከላከል ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል