የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ “ነጻነታቸውን የተነፈጉ ሰዎች ሰብአዊ መብቶች የሚጣሱባቸውን ዐውዶች በመመርመር፣ የጥሰት መንስኤዎችን እልባት ለመስጠት፣ ጥሰቶችን ለማስቆም፣ በጥሰቶች ተሳታፊ የሆኑ አጥፊዎችን ተጠያቂነት ለማረጋገጥ እና ለተጎጂዎች ተገቢ የሆነውን የካሳ ሥርዓት ለመዘርጋት እንዲሁም ይህንኑ በሥራ ላይ ለማዋል የፌዴራል እና የክልል መንግሥታት ቁርጠኛ ሊሆኑ ይገባል” ብለዋል
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ለአምስት ዓመታት በአማራ፣ ኦሮሚያ፣ ሶማሌ እና የቀድሞ ደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልሎች ያካሄደውን የዜጎች ነጻነት የተመለከተ ብሔራዊ ምርመራ ይፋ አደረገ
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ከሚያዝያ 2010 ዓ.ም. እስከ ሚያዝያ 2015 ዓ.ም. ባሉት አምስት ዓመታት ነጻነታቸውን በተነፈጉ ሰዎች መብቶች ዙሪያ በአራት ክልሎች ባከናወናቸው 4 ብሔራዊ ምርመራ /National Inquiry/ የተገኙ ዋና ዋና ግኝቶችን እና ምክረ ሐሳቦችን ያጠናቀረ ባለ 130 ገጽ ሪፖርት ዛሬ ይፋ አድርጓል
የፌዴራል እና የክልል መንግሥታት ነጻነታቸውን የተነፈጉ ሰዎች ሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችን ለማስቆም፣ በጥሰቶች ተሳታፊ የሆኑ አጥፊዎችን ተጠያቂ ለማድረግ እና ለተጎጂዎች ተገቢ የሆነውን የካሳ ሥርዓት ለመዘርጋት ቁርጠኛ ሊሆኑ ይገባል
ይህን ያለው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን በአስገዳጅ ሁኔታ ከጎዳና ላይ እያፈሱ ወደ ሌላ ቦታ የመውሰዱ አሰራር በአስቸኳይ እንዲቆም አሳስቧል
በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ገላን ክፍለ ከተማ ውስጥ በሚገኝ ጊዜያዊ የሰዎች ማቆያ ስፍራ በተላላፊ በሽታ ምክንያት የሦስት ሰዎች ሕይወት ማለፉን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አስታወቀ። የኦሮሚያ ክልል በበኩሉ በክልሉ የሰዎች ማቆያ ስፍራ አለመኖሩን ይገልጻል
የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባል አቶ ክርስቲያን ታደለን፣ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ ም/ቤት አባል አቶ ዮሐንስ ቧያለውን፣ የአዲስ አበባ ከተማ ም/ቤት አባል ዶ/ር ካሣ ተሻገርን ጨምሮ 53 ሰዎች አዋሽ አርባ ውስጥ ባለ የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የምዕራብ ዕዝ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ካምፕ መታሰራቸው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን አረጋገጠ
ኮሚሽኑ ይህን ያለው ዋና ኮሚሽነሩ ዳንዔል በቀለን ጨምሮ አምስት የኮሚሽኑ ባለሙያዎች የሚገኙበት ቡድን በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መሠረት በቁጥጥር ሥር ውለው አዋሽ አርባ አካባቢ በሚገኘው የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የምዕራብ ዕዝ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ካምፕ ውስጥ ተይዘው የሚገኙትን ታሳሪዎች ነሐሴ 26 ቀን 2015 ዓ.ም. መጎብኘቱን አስመልክቶ ዛሬ ነሐሴ 27 ባወጣውና ለአሻም በላከላት መግለጫ ላይ ነው
VOA News - Detention - Addis Ababa The Ethiopian Human Rights Commission has called for an end to what it calls a rising trend of enforced disappearances in the country
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ፣ የዮናስ ብርሃነን መታሰር አስመልክተው፣ ትላንት ሰኔ አራት ቀን፣ በማኅበራዊ ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፣ “ድርጊቱ ሕገ ወጥ እና ተቀባይነት የሌለው ነው፤” ሲሉ ኮንነዋል