Skip to content
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Ethiopian Human Rights Commission – EHRC
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
        • Regions

          EHRC is an independent federal institution tasked with the promotion and protection of human rights in Ethiopia.

        • Addis Ababa
        • Afar
        • Amhara
        • Benishangul Gumuz
        • Gambella
        • Oromia
        • Somali
        • Tigray
        • Central Ethiopia
        • Dire Dawa
        • Harari
        • Sidama
        • South Ethiopia
        • South West Ethiopia Peoples'
  • Areas of Work
        • Areas of Work

          We are an independent national human rights institution tasked with the promotion & protection of human rights in Ethiopia.

        • Economic, Social & Cultural Rights
        • Civil & Political Rights
        • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
        • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
        • Women’s & Children’s Rights
        • Human Rights Education
        • Human Rights Monitoring & Investigation
        • Human Rights Film Festival
        • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
 
Ethiopian Human Rights Commission – EHRCEthiopian Human Rights Commission – EHRC

በአሳሳቢ ሁኔታ ላይ የሚገኘውን ትምህርት የማግኘት መብት በተመለከተ የተካሄደ የምክክር መድረክ

August 8, 2024August 9, 2024 Event Update

የ2017 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን መቃረብን ከግንዛቤ ያስገባ ፈጣን እና የተቀናጀ የመፍትሔ እርምጃ መውሰድ አስፈላጊ ነው

Twitter Facebook Telegram Email Whatsapp Print

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በተለያዩ ክልሎች ትምህርት የማግኘት መብት አፈጻጸምን በተመለከተ ባሉ አሳሳቢ ሁኔታዎች እና ሊወሰዱ በሚገባቸው የመፍትሔ እርምጃዎች ላይ ሐምሌ 11 ቀን 2016 ዓ.ም. ከባለድርሻ አካላት ጋር በአዲስ አበባ ከተማ ምክክር አካሂዷል። በውይይት መድረኩ ላይ የትምህርት ሚኒስቴር፣ የክልል ትምህርት ቢሮዎች እንዲሁም የሴቶች እና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴርን ጨምሮ የሌሎች መንግሥታዊ እና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት ተወካዮች ተሳትፈዋል።  

በውይይቱ ላይ ትምህርት የማግኘት መብት በተለያዩ ዓለም አቀፋዊ፣ አህጉራዊና ብሔራዊ የሰብአዊ መብቶች ሕጎች መሠረት ያለው ጥበቃ፣ ተያያዥ የመንግሥት ግዴታዎች እንዲሁም ኢሰመኮ በተለያዩ ክልሎች የመብቱን አፈጻጸም በተመለከተ ያሰባሰበው መረጃ ቀርቧል። በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በተከሰቱና በቀጠሉ ግጭቶች፣ የተፈጥሮ አደጋዎች እና ተያያዥ መፈናቀሎች ምክንያት ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሕፃናት ከትምህርት ገበታ ውጭ ሲሆኑ በርካታ ትምህርት ቤቶችም ከአገልግሎት ውጪ ሆነዋል። ለምሳሌ በአማራ ክልል 4178፣ በትግራይ ከልል 648፣ በኦሮሚያ ክልል 420፣ በሶማሊ ክልል 195፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል 50፣ በጋምቤላ ክልል 40፣ በአፋር ክልል 26 እንዲሁም በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል 8 ትምህርት ቤቶች መዘጋታቸውን ኢሰመኮ ያሰባሰበው መረጃ ያመለክታል።

የኢሰመኮ ተጠባባቂ ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ ለምክክር መድረኩ ተሳታፊዎች ንግግር ሲያደርጉ

በተጨማሪም አንጻራዊ ሰላም ባለባቸው እንደ ደቡብ ኢትዮጵያ እና ማእከላዊ ኢትዮጵያ ያሉ ክልሎች ውስጥ የመምህራን ደመወዝ በወቅቱ እና በአግባቡ ባለመከፈሉ የመማር ማስተማር ሂደቱ በበርካታ ትምህርት ቤቶች ተስተጓጉሏል። በተመሳሳይ በሰው ሠራሽ እና የተፈጥሮ አደጋዎች ምክንያት የተፈናቀሉ ሰዎች በሚኖሩባቸው አካባቢዎች የሚገኙ ትምህርት ቤቶች በመዘጋታቸው ምክንያት በርካታ ተፈናቃይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ ሆነዋል። ይህንን ተከተሎም ሕፃናት በተለይም ሴት ሕፃናት ከትምህርት መብት በተጨማሪ ያለ ዕድሜ ጋብቻን ጨምሮ ለሌሎች ዘርፈ ብዙ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች እና ጥቃቶች ተጋላጭ መሆናቸው፣ ወደ ከተማ እየፈለሱና ለጉልበት ብዝበዛ እየተዳረጉ መሆኑ፣ ለተለያዩ ሱሶች እንዲሁም ሥነ-ልቦናዊ፣ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳቶች መጋለጣቸው በውይይቱ ተገልጿል።

የመድረኩ ተሳታፊዎች በተለያዩ ምክንያቶች የወደሙ ትምህርት ቤቶችን መልሶ ለመገንባት እና ከትምህርት ገበታ ውጪ የሆኑ ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ለመመለስ እየተወሰዱ ስላሉ እና በቀጣይ ሊወሰዱ ስለሚገባቸው እርምጃዎች ተወያይተዋል። በዋነኝነት ችግሩን ለመፍታት በትጥቅ ግጭትም ሆነ በተፈጥሮ አደጋ ምክንያት ከትምህርት ገበታ ውጪ የሆኑ ተማሪዎች ወደ ትምህርት እንዲመለሱ አስቻይ ሁኔታዎችን መፍጠር፤ በግጭት ምክንያት የወደሙ ትምህርት ቤቶችን መልሶ ለማቋቋም በቂ በጀት የተያዘላቸውና በዕቅድ ውስጥ የተካተቱ መሆናቸውን ማረጋገጥ፤ ትምህርት ቤቶች በቋሚነት እስኪገነቡ ድረስ ጊዜያዊ የመማሪያ አማራጮችን ማዘጋጀት፤ ሕፃናት እና መምህራንን ጨምሮ የትምህርት ማኅበረሰቡ አባላት የሥነ-ልቦና እና ማኅበራዊ ድጋፍ የሚያገኙበትን ሁኔታ ማመቻችት፤ በመፈናቀል ዐውድ ውስጥ ለሚገኙ ተማሪዎች የትምህርት ቤት የምገባ መርኃ ግብር ማስጀመር እንዲሁም ትምህርት ቤቶችን መጠለያ ላደረጉ ተፈናቃዮች ዘላቂ መፍትሔ በማመቻቸት በመጠለያነት እያገለገሉ ያሉ የትምህርት ተቋማት የትምህርት አገልግሎት እንዲቀጥሉ ለማድረግ አዎንታዊ እርምጃዎችን መውሰድ እንደሚገባ መግባባት ላይ ተደርሷል።

የኢሰመኮ ተጠባባቂ ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ ለምክክር መድረኩ ተሳታፊዎች ንግግር ሲያደርጉ

የኢሰመኮ የሴቶች፣ የሕፃናት፣ የአረጋውያን እና የአካል ጉዳተኞች መብቶች ኮሚሽነር ርግበ ገብረሐዋሪያ፣ ትምህርት የማግኘት መብትን በማረጋገጥ ረገድ መንግሥት ግንባር ቀደም ባለግዴታ መሆኑን በአጽንዖት ጠቅሰው፣ በተለይም የ2017 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን እየተቃረበ መሆኑን ከግንዛቤ በማስገባት መንግሥታዊ እና መንግሥታዊ ያልሆኑ ባለድርሻ አካላት በትብብር እንዲሠሩ እና በአሳሳቢ ሁኔታ ላይ የሚገኘው የትምህርት መብት አፋጣኝ መፍትሔ እንዲሰጠው የበኩላቸውን አስተዋጽዖ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል። 

Related posts

March 25, 2023March 25, 2023 Event Update
አካታች፣ ተደራሽ እና ተቀባይነት ያለው የመማር ዕድል ለሀገር ውስጥ ተፈናቃይ ሕፃናት
February 29, 2024February 29, 2024 Event Update
ለአራተኛው ሀገር አቀፍ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሰብአዊ መብቶች ምስለ ችሎት ውድድር ማስጀመሪያ ውይይት ከትምህርት ቢሮ አስተባባሪዎች ጋር ተካሄደ
June 12, 2024June 12, 2024 Event Update
በወንጀል ነክ ነገር ውስጥ ገብተው በማቆያና ተሐድሶ ተቋም ውስጥ የሚገኙ ሕፃናት (ከ9 – 15 ዓመት) የሰብአዊ  መብቶች ሁኔታ ክትትል ግኝቶች ላይ የተካሄደ ውይይት
July 22, 2024July 22, 2024 Event Update
ቤኒሻንጉል ጉሙዝ፦ በድኅረ ግጭት ዐውድ የእናቶችና የጨቅላ ሕፃናት የጤና መብቶች ሁኔታ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር የተካሄደ ውይይት 

Signup for the Latest Update from EHRC

Submit your email to singup
Facebook Like us on FacebookXFollow us on XYouTube Follow us on YouTubeLinkedin Follow us on LinkedinWhatsApp WhatsAppTikTok TikTokTelegram TelegramInstagram InstagramFlicker Flickr

Useful Links

  • NANHRI
  • GANHRI
  • OHCHR
  • ACHPR
  • TRANSITIONAL JUSTICE

Get Involved

  • Jobs
  • Events
  • Contact Us
  • Telegram Bot
  • Subscribe to our newsletter

Connect with Us

  • Facebook
  • Twitter
  • LinkedIn
  • YouTube
  • Flickr
  • Instagram
Descriptive Text

We are an independent
national human rights
institution tasked with
the promotion and protection of human
rights in Ethiopia.

Submit your email to get the latest update from EHRC

Address: Sunshine Tower No. 5, Meskel Square, on Bole Road next to Hyatt Regency Hotel, Addis Ababa, Ethiopia
Tel: +251115504031 | Fax: +251 11 550 4125 | PO Box 1165 Addis Ababa | Email: info@ehrc.org


The contents of this website, excepting third party content for which the Commission bears no responsibility,
may be freely used and copied for educational and other non-commercial purposes, provided that any such reproduction is accompanied by an acknowledgement of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC). Source of images used in the content of this website: EHRC Media and Communications Department Archive and Creative Common License.

This website is managed by the Media and Communications team of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC).

We are using cookies to give you the best experience on our website.

You can find out more about which cookies we are using or switch them off in .

Scroll to top
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
    • Addis Ababa
    • Afar
    • Amhara
    • Benishangul Gumuz
    • Central Ethiopia
    • Dire Dawa
    • Gambella
    • Harari
    • Oromia
    • Sidama
    • Somali
    • South Ethiopia
    • South West Ethiopia Peoples’
    • Tigray
  • Areas of Work
    • Economic, Social & Cultural Rights
    • Civil & Political Rights
    • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
    • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
    • Human Rights Monitoring & Investigation
    • Women’s & Children’s Rights
    • Human Rights Education
    • Human Rights Film Festival
    • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Search
Ethiopian Human Rights Commission - EHRC
Powered by  GDPR Cookie Compliance
Privacy Overview

This website uses cookies so that we can provide you with the best user experience possible. Cookie information is stored in your browser and performs functions such as recognising you when you return to our website and helping our team to understand which sections of the website you find most interesting and useful.

Strictly Necessary Cookies

Strictly Necessary Cookie should be enabled at all times so that we can save your preferences for cookie settings.

If you disable this cookie, we will not be able to save your preferences. This means that every time you visit this website you will need to enable or disable cookies again.