Skip to content
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Ethiopian Human Rights Commission – EHRC
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
        • Regions

          EHRC is an independent federal institution tasked with the promotion and protection of human rights in Ethiopia.

        • Addis Ababa
        • Afar
        • Amhara
        • Benishangul Gumuz
        • Gambella
        • Oromia
        • Somali
        • Tigray
        • Central Ethiopia
        • Dire Dawa
        • Harari
        • Sidama
        • South Ethiopia
        • South West Ethiopia Peoples'
  • Areas of Work
        • Areas of Work

          We are an independent national human rights institution tasked with the promotion & protection of human rights in Ethiopia.

        • Economic, Social & Cultural Rights
        • Civil & Political Rights
        • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
        • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
        • Women’s & Children’s Rights
        • Human Rights Education
        • Human Rights Monitoring & Investigation
        • Human Rights Film Festival
        • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
 
Ethiopian Human Rights Commission – EHRCEthiopian Human Rights Commission – EHRC

በኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ የሚሠሩ ሴት ሠራተኞች የሰብአዊ መብቶች አያያዝ እንዲሻሻል ባለግዴታዎች የበኩላቸውን ድርሻ የመወጣት ኃላፊነት አለባቸው

October 3, 2022October 5, 2022 Event Update

ኢሰመኮ በአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ የሴት ሠራተኞች የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ድኅረ ክትትል ግኝቶች ያቀረባቸው ምክረ ሃሳቦች ተፈጻሚነታቸው ሊረጋገጥ ይገባል

Twitter Facebook Telegram Email Whatsapp Print

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በአዳማ የኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ በመሥራት ላይ የሚገኙ ሴት ሠራተኞች የሰብአዊ መብቶች አያያዝን በተመለከተ በሰኔ ወር 2014 ዓ.ም. የመጀመሪያ ሳምንት በተደረገው ድኅረ ክትትል የተለዩ ግኝቶች ላይ መስከረም 6 ቀን 2015 ዓ.ም. በቢሾፍቱ ከተማ ከመንግሥት አስፈጻሚ አካላት፣ ከአዳማ ከተማ የፖሊስ አካላት፣ ከሚመለከታቸው ሲቪል ማኅበራት፣ የኢንዱስትሪ ፓርክ አስተዳደር ኃላፊዎች፣ የአሠሪዎችና የሠራተኞች ማኅበራት ፌዴሬሽኖች እና የዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር ውይይት አካሂዷል።

በድኅረ ክትትል ግኝቶች ላይ በተካሄደው ውይይት በክትትሉ የተለዩ ጠንካራና ትኩረት የሚሹ ክፍተቶች ለተሳታፊዎች ቀርበዋል፡፡ በጠንካራ ጎን ከተነሱት መካከል፣ ሠራተኞች የማኅበራዊ ዋስትና ተጠቃሚ መሆናቸው፣ የመደራጀት መብትን ለማስከበር በጎ ጅምሮች መኖራቸው፣ ከወሲባዊና ሥነ ተዋልዶ ጤና እንዲሁም የሕይወት ክህሎት ጋር የተያያዘ መረጃ የማግኘት መብትን ለማስጠበቅ መሠራቱ እና በፓርኩ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለሟሟላት በተለያዩ ተቋማት ቢሮዎች መመቻቸታቸው የሚጠቀሱ ናቸው። 

በሌላጎኑ በመንግሥት አካላት መደረግ ያለበት ቁጥጥር አነስተኛ መሆኑ፣ በጨርቃ ጨርቅ እና አልባሳት ኢንዱስትሪ ዘርፉ የጤና ጉዳት የሚያስከትሉ ሥራዎችን ለመለየት የሚያስችሉ አሠራሮች አለመዘርጋት፣ ሕግን ያልተከተለ የሴት ሠራተኞች ቅነሳ መደረጉ እና ለትርፍ ሰዓት ሥራ የሚከፈለዉ ክፍያ አነስተኛና አስገዳጅ መሆኑ ውይይት ከተደረግባቸው ክፍተቶች መካከል ተጠቃሽ ናቸው። በተጨማሪም ለነፍሰ ጡርና ለወለዱ ሴት ሠራተኞች የሚደረገው ድጋፍ በቂ አለመሆኑ፣ ከወሊድ በኋላ አብዛኞቹ ሴቶች ወደ ሥራ የማይመለሱ መሆኑ፣  በአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ላይ የተመለከተው የዝቅተኛ ደመወዝ ወሳኝ ቦርድ ተቋቁሞ ወደ ሥራ እንዲገባ አለመደረጉ በድኅረ ክትትሉ የተለዩ እና ሰፊ ውይይት የተደረገባቸው ሌሎች ዋና ዋና ግኝቶች ናቸው፡፡ 

የኢሰመኮ የሴቶችና ሕፃናት መብቶች ሥራ ክፍል ዳይሬክተር ላምሮት ፍቅሬ በዝግጅቱ ላይ ባደረጉት ንግግር በኮሚሽኑ የክትትል ግኝቶችና በውይይት የተገኙ ግብዓቶችን መነሻ በማድረግ በቀጣይ የተለያዩ ስልቶችን በመጠቀም የማስተካከያ እርምጃዎች እንዲወሰዱ ምክረ ሃሳብ ሰጥተዋል። አክለውም በሕግ የተቀመጡ የሴት ሠራተኞች መብቶችን ማክበር፣ ማስከበር እና ማሟላት ላይ ትኩረት በመስጠት ባለግዴታ አካላት ከተሰጣቸው ሥልጣንና ኃላፊነት በመነሳት የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ ጥሪ አድርገዋል።

በተካሄደው የምክክር መድረክም በክትትሉ ግኝቶችና ምክረ ሃሳቦች መሠረት በቀጣይ እያንዳንዱ ባለግዴታ አካላት መሥራት ባለባቸው ጉዳዮች ላይ የወደፊት አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡

በዚህም መሰረት በኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ የሚሠሩ ሴት ሠራተኞች መብቶች አያያዝን ለማሻሻል የሠራተኞቹ የመደራጀት መብት ሕጉን እና ሥርዓቱን ተከትሎ በተሟላ ሁኔታ እንዲከበር፣ የሠራተኛ እና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር እና በተዋረድ የሚገኙ ቢሮዎች በፓርኩ ውስጥ በሚገኙ ፋብሪካዎች ላይ ተገቢ የሆነ መደበኛ ቁጥጥር ለማድረግ እና እርምት ለመውሰድ የሚያስችል አሠራር መዘርጋት እንዳለባቸው ተመላክቷል፡፡ በአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ላይ የተመለከተው የዝቅተኛ ደሞዝ ወሳኝ ቦርድ ተቋቁሞ ወደ ሥራ እንዲገባ በማድረግ የሴት ሠራተኞች በቂ ክፍያ የማግኘት መብት ላይ ያላቸውን የመደራደር አቅም ማሳደግ እንደሚገባም ተገልጿል። 

በተመሳሳይ መልኩ ባለግዴታ አካላት የቁጥጥር መስፈርቶችን በማዘጋጀት የሥራ መደቦቹ የሚያስፈልጋቸውን የደኅንነት መጠበቂያ ቁሳቁሶችና ሌሎች ተጨማሪ ድጋፎች በመለየት የቁጥጥር ሥራ መሥራት እንዳለባቸው፣ ሴት ሠራተኞች የወሲባዊና ሥነ ተዋልዶ ጤና መብቶችን የሚመለከቱ መረጃዎችና አገልግሎቶች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለሁሉም ሴት ሠራተኞች ስልጠና የሚያገኙበት አሠራር መዘርጋት እንዳለበት ተገልጿል፡፡ የቤተሰብ ምጣኔ አገልግሎቶች ተደራሽነትን ማረጋገጥ፣ የነፍሰ ጡር እናቶች የጤና ክትትልን ማሻሻል፣ የወለዱ እናቶች ሥራቸውን የሚያቋርጡበትን ምክንያት በተመለከተ በባለግዴታ አካላት ጥናት መደረግ እንዳለበት እና በአጠቃላይ የሴት ሠራተኞችን መብቶች አያያዝ ለማሻሻል ባለግዴታ አካላት ሰፊ ሥራ የሚጠበቅባቸው መሆኑን አጽንዖት በመስጠት የውይይት መድረኩ ተጠናቋል፡፡

Related posts

December 29, 2022August 28, 2023 Event Update
በግል ሥራ እና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች ተቀጥረው የሚሠሩ ሠራተኞች የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ክትትል ሪፖርት የቀረቡ ምክረ ሃሳቦችን ተፈጻሚነት ለማረጋገጥ ኮሚሽኑ ቀጣይነት ያለው የውትወታ ሥራዎች ይሠራል
June 13, 2023August 28, 2023 Event Update
በግንባታ ዘርፍ ደኅንነቱ የተጠበቀ እና ጤናማ የሥራ ሁኔታ መብት አተገባበር
June 10, 2023June 11, 2023 Event Update
በአዲስ አበባ በሚገኙ የሕፃናት ማሳደጊያ ማእከላት በተከናወነ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ክትትል ሪፖርት ላይ የተካሄደ ውይይት
October 12, 2023August 8, 2024 Event Update
ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ፡- የጤና መብት እና የግንባታ ዘርፍ ደኅንነቱ የተጠበቀና ጤናማ የሥራ ሁኔታ መብት አተገባበር ክትትል ሪፖርቶችን መሠረት ያደረጉ የውትወታ መድረኮች ተካሄዱ

Signup for the Latest Update from EHRC

Submit your email to singup
Facebook Like us on FacebookXFollow us on XYouTube Follow us on YouTubeLinkedin Follow us on LinkedinWhatsApp WhatsAppTikTok TikTokTelegram TelegramInstagram InstagramFlicker Flickr

Useful Links

  • NANHRI
  • GANHRI
  • OHCHR
  • ACHPR
  • TRANSITIONAL JUSTICE

Get Involved

  • Jobs
  • Events
  • Contact Us
  • Telegram Bot
  • Subscribe to our newsletter

Connect with Us

  • Facebook
  • Twitter
  • LinkedIn
  • YouTube
  • Flickr
  • Instagram
Descriptive Text

We are an independent
national human rights
institution tasked with
the promotion and protection of human
rights in Ethiopia.

Submit your email to get the latest update from EHRC

Address: Sunshine Tower No. 5, Meskel Square, on Bole Road next to Hyatt Regency Hotel, Addis Ababa, Ethiopia
Tel: +251115504031 | Fax: +251 11 550 4125 | PO Box 1165 Addis Ababa | Email: info@ehrc.org


The contents of this website, excepting third party content for which the Commission bears no responsibility,
may be freely used and copied for educational and other non-commercial purposes, provided that any such reproduction is accompanied by an acknowledgement of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC). Source of images used in the content of this website: EHRC Media and Communications Department Archive and Creative Common License.

This website is managed by the Media and Communications team of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC).

We are using cookies to give you the best experience on our website.

You can find out more about which cookies we are using or switch them off in .

Scroll to top
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
    • Addis Ababa
    • Afar
    • Amhara
    • Benishangul Gumuz
    • Central Ethiopia
    • Dire Dawa
    • Gambella
    • Harari
    • Oromia
    • Sidama
    • Somali
    • South Ethiopia
    • South West Ethiopia Peoples’
    • Tigray
  • Areas of Work
    • Economic, Social & Cultural Rights
    • Civil & Political Rights
    • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
    • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
    • Human Rights Monitoring & Investigation
    • Women’s & Children’s Rights
    • Human Rights Education
    • Human Rights Film Festival
    • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Search
Ethiopian Human Rights Commission - EHRC
Powered by  GDPR Cookie Compliance
Privacy Overview

This website uses cookies so that we can provide you with the best user experience possible. Cookie information is stored in your browser and performs functions such as recognising you when you return to our website and helping our team to understand which sections of the website you find most interesting and useful.

Strictly Necessary Cookies

Strictly Necessary Cookie should be enabled at all times so that we can save your preferences for cookie settings.

If you disable this cookie, we will not be able to save your preferences. This means that every time you visit this website you will need to enable or disable cookies again.