Skip to content
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Ethiopian Human Rights Commission – EHRC
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
        • Regions

          EHRC is an independent federal institution tasked with the promotion and protection of human rights in Ethiopia.

        • Addis Ababa
        • Afar
        • Amhara
        • Benishangul Gumuz
        • Gambella
        • Oromia
        • Somali
        • Tigray
        • Central Ethiopia
        • Dire Dawa
        • Harari
        • Sidama
        • South Ethiopia
        • South West Ethiopia Peoples'
  • Areas of Work
        • Areas of Work

          We are an independent national human rights institution tasked with the promotion & protection of human rights in Ethiopia.

        • Economic, Social & Cultural Rights
        • Civil & Political Rights
        • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
        • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
        • Women’s & Children’s Rights
        • Human Rights Education
        • Human Rights Monitoring & Investigation
        • Human Rights Film Festival
        • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
 
Ethiopian Human Rights Commission – EHRCEthiopian Human Rights Commission – EHRC

በግል ሥራ እና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች ተቀጥረው የሚሠሩ ሠራተኞች የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ክትትል ሪፖርት የቀረቡ ምክረ ሃሳቦችን ተፈጻሚነት ለማረጋገጥ ኮሚሽኑ ቀጣይነት ያለው የውትወታ ሥራዎች ይሠራል

December 29, 2022August 28, 2023 Event Update

የሠራተኞች መብቶችን አፈጻጸም በበላይነት የማረጋገጥ ኃላፊነት የመንግሥት ቢሆንም ሌሎች የሚመለከታቸው አካላትም ኢሰመኮ በክትትል ሪፖርቱ ያቀረባቸውን ምክረ-ሃሳቦች ለመተግበር በጋራ መሥራት ይጠበቅባቸዋል

Twitter Facebook Telegram Email Whatsapp Download Print

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በግል ሥራ እና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲ ሠራተኞች ላይ የተሠሩ ጥናቶችን እና የቀረቡለትን በርካታ ቅሬታዎችን መሠረት በማድረግ በግል ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲ ሠራተኞች ሰብአዊ መብቶች አተገባበር ዙሪያ ያከናወነውን የክትትል ሥራ ሪፖርት ኅዳር 2 ቀን 2015 ዓ.ም. ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። በሪፖርቱ የተካተቱ ግኝቶች እና ምክረ ሃሳቦች አፈጻጸምን በተመለከተ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በአራት ከተሞች ማለትም በአዲስ አበባ፣ በባሕር ዳር፣ በሃዋሳ እና በጅማ  ተከታታይ የምክክር መድረኮች ተካሂደዋል። 

በመድረኮቹ ላይ ከፍርድ ቤቶች፣ አግባብነት ካላቸው የአስፈጻሚ አካላት፣ ከሠራተኛ ማኅበራት፣ ከአሠሪዎች፣ ከግል ሥራ እና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች፣ እንዲሁም ከሲቪል ማኅበራት የተውጣጡ አካላት ተሳትፈዋል።

በምክክር መድረኮቹ በሪፖርቱ የተለዩ የክትትል ግኝቶች እና የተሰጡ ምክረ-ሃሳቦች በኮሚሽኑ የሰብአዊ መብቶች ባለሞያዎች የቀረቡ ሲሆን በኢትዮጵያ የሠራተኞች ሰብአዊ መብቶችን የሚመለከቱ የሕግ ማዕቀፎችን የተመለከተ ገለጻ ለተሳታፊዎች ቀርቧል። የኤጀንሲ ሠራተኞች መብቶች በተለይም ምቹ የሥራ ሁኔታዎችን የማግኘት፣ እኩልነትና ከአድልዎ ነጻ የመሆን፣ የሥራ ዋስትና የማግኘት፣ ማኅበራዊ ዋስትና የማግኘት፣ የመደራጀት፣ ቅሬታ የማሰማት እንዲሁም ፍትሕ የማግኘት መብቶች እየተጣሱ እንደሆነ በመድረኮቹ ተነስቷል፡፡ እነዚህ ጉዳዮችን መሠረት በማድረግ ከሠራተኞች መብቶች ጋር በተገናኘ የሚስተዋሉ ችግሮችን እንዴት መቅረፍ ይቻላል፣ የክትትል ሪፖርቱ ከወጣ በኋላ ስለተወሰዱ እርምጃዎች እና በቀጣይም ከእያንዳንዱ ባለድርሻ አካላት ምን ይጠበቃል በሚሉ ጉዳዮች ላይ ከተሳታፊዎች ጋር ውይይት ተደርጓል። 

የኢሰመኮ የሲቪል እና ፖለቲካ፣ የማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መብቶች ኮሚሽነር ዶ/ር አብዲ ጅብሪል በመድረኮቹ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር፤ መድረኮቹ የተዘጋጁት በክትትል ሪፖርቱ የተገኙትን ግኝቶች እና የተሰጡትን ምክረ-ሃሳቦች በመተግበር የግል ሥራ እና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲ ሠራተኞች የሰብአዊ መብቶችን በተሻለ ሁኔታ ተግባራዊ እንዲሆኑ ለማስቻል ያለመ እንደሆነ ገልጸው፤ ሀገሪቱ የሠራተኞች የሰብአዊ መብቶችን በሚመለከት በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ሕገ-መንግሥት ውስጥ ከማካተትም በላይ ዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ፣ ማኅበራዊና ባህላዊ መብቶች ቃል ኪዳንን፣ አግባብነት ያላቸው የዓለም ሥራ ድርጅት ስምምነቶችን እና የተለያዩ የሠራተኞች መብቶችን የሚመለከቱ ዓለም አቀፍ ስምምነቶችን ተቀብላ ማጽደቋን አብራርተዋል። አክለውም መንግሥት እና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት በእነዚህ የሰብአዊ መብቶች የሕግ ማዕቀፎች ለተደነገጉት የሠራተኞች መብቶች መከበር እና መረጋገጥ እንዲሠሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡  

Related posts

June 30, 2022October 6, 2022 Event Update
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የግል ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች እና ሰብአዊ መብቶች በኢትዮጵያ በሚል ርዕስ ዙሪያ የውይይት መድረክ አካሄደ
November 11, 2022November 11, 2022 Press Release
የሥራ እና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች አሠራር ሰብአዊ መብቶችን ሊያከብር ይገባል
October 3, 2022October 5, 2022 Event Update
በኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ የሚሠሩ ሴት ሠራተኞች የሰብአዊ መብቶች አያያዝ እንዲሻሻል ባለግዴታዎች የበኩላቸውን ድርሻ የመወጣት ኃላፊነት አለባቸው
October 18, 2023October 23, 2023 Event Update
በምግብ ሥርዓት፣ ምግብ የማግኘት መብት እና ሰብአዊ መብትን መሠረት ያደረገ አቀራረብ ዙሪያ የተካሄዱ ስልጠናዎች

Signup for the Latest Update from EHRC

Submit your email to singup
Facebook Like us on FacebookXFollow us on XYouTube Follow us on YouTubeLinkedin Follow us on LinkedinWhatsApp WhatsAppTikTok TikTokTelegram TelegramInstagram InstagramFlicker Flickr

Useful Links

  • NANHRI
  • GANHRI
  • OHCHR
  • ACHPR
  • TRANSITIONAL JUSTICE

Get Involved

  • Jobs
  • Events
  • Contact Us
  • Telegram Bot
  • Subscribe to our newsletter

Connect with Us

  • Facebook
  • Twitter
  • LinkedIn
  • YouTube
  • Flickr
  • Instagram
Descriptive Text

We are an independent
national human rights
institution tasked with
the promotion and protection of human
rights in Ethiopia.

Submit your email to get the latest update from EHRC

Address: Sunshine Tower No. 5, Meskel Square, on Bole Road next to Hyatt Regency Hotel, Addis Ababa, Ethiopia
Tel: +251115504031 | Fax: +251 11 550 4125 | PO Box 1165 Addis Ababa | Email: info@ehrc.org


The contents of this website, excepting third party content for which the Commission bears no responsibility,
may be freely used and copied for educational and other non-commercial purposes, provided that any such reproduction is accompanied by an acknowledgement of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC). Source of images used in the content of this website: EHRC Media and Communications Department Archive and Creative Common License.

This website is managed by the Media and Communications team of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC).

We are using cookies to give you the best experience on our website.

You can find out more about which cookies we are using or switch them off in .

Scroll to top
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
    • Addis Ababa
    • Afar
    • Amhara
    • Benishangul Gumuz
    • Central Ethiopia
    • Dire Dawa
    • Gambella
    • Harari
    • Oromia
    • Sidama
    • Somali
    • South Ethiopia
    • South West Ethiopia Peoples’
    • Tigray
  • Areas of Work
    • Economic, Social & Cultural Rights
    • Civil & Political Rights
    • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
    • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
    • Human Rights Monitoring & Investigation
    • Women’s & Children’s Rights
    • Human Rights Education
    • Human Rights Film Festival
    • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Search
Ethiopian Human Rights Commission - EHRC
Powered by  GDPR Cookie Compliance
Privacy Overview

This website uses cookies so that we can provide you with the best user experience possible. Cookie information is stored in your browser and performs functions such as recognising you when you return to our website and helping our team to understand which sections of the website you find most interesting and useful.

Strictly Necessary Cookies

Strictly Necessary Cookie should be enabled at all times so that we can save your preferences for cookie settings.

If you disable this cookie, we will not be able to save your preferences. This means that every time you visit this website you will need to enable or disable cookies again.