Skip to content
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Ethiopian Human Rights Commission – EHRC
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
        • Regions

          EHRC is an independent federal institution tasked with the promotion and protection of human rights in Ethiopia.

        • Addis Ababa
        • Afar
        • Amhara
        • Benishangul Gumuz
        • Gambella
        • Oromia
        • Somali
        • Tigray
        • Central Ethiopia
        • Dire Dawa
        • Harari
        • Sidama
        • South Ethiopia
        • South West Ethiopia Peoples'
  • Areas of Work
        • Areas of Work

          We are an independent national human rights institution tasked with the promotion & protection of human rights in Ethiopia.

        • Economic, Social & Cultural Rights
        • Civil & Political Rights
        • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
        • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
        • Women’s & Children’s Rights
        • Human Rights Education
        • Human Rights Monitoring & Investigation
        • Human Rights Film Festival
        • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
 
Ethiopian Human Rights Commission – EHRCEthiopian Human Rights Commission – EHRC

ሰብአዊ ክብር፣ ነጻነት እና ፍትሕ ለሁሉም:- የኢሰመኮ የሰብአዊ መብቶች ዓመታዊ ፊልም ፌስቲቫል ሁለተኛ ዙር በአዳማ፣ በአዲስ አበባ፣ በባሕር ዳር፣ በሃዋሳ እና በጅግጅጋ ይካሄዳል

December 10, 2022September 9, 2024 2nd Film Festival, Press Release

ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ቀንን ለማሰብ እና የሰብአዊ መብቶች ግንዛቤ ለማዳበር ሰፊ ተደራሽነት ያለውን የፊልም ጥበብን በመጠቀም በሰብአዊ መብቶች ጉዳይ ላይ የሚያጠነጥኑ ፊልሞች ለእይታ እና ለውይይት ይቀርባሉ

Twitter Facebook Telegram Email Whatsapp Print

በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አዘጋጅነት ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ቀንን ለማሰብ የተጀመረው ዓመታዊ የሰብአዊ መብቶች ፊልም ፌስቲቫል ለመጀመሪያ ጊዜ ከኅዳር 28 እስከ ታኅሣሥ 4 ቀን 2014 ዓ.ም. በአዳማ፣ በአዲስ አበባ እና በሃዋሳ ከተሞች መካሄዱ ይታወሳል። ዘንድሮ ለሁለተኛ ጊዜ አዲስ አበባን ጨምሮ በአምስት ከተሞች የሚካሄደው የሰብአዊ መብቶች ፊልም ፌስቲቫል ታኅሣሥ 1 ቀን 2015 ዓ.ም. በይፋ ጀምሯል።

ሰብአዊ ክብር፣ ነጻነት እና ፍትሕ ለሁሉም በሚል መሪ ቃል የሚከበረውን የዘንድሮውን ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ቀንን ምክንያት በማድረግ ሰፊ ተደራሽነት ያለውን የፊልም ጥበብን በመጠቀም እና ስለ ሰብአዊ መብቶች ያለውን ግንዛቤ ለማዳበር በሰብአዊ መብቶች ጉዳይ ላይ የሚያጠነጥኑ ፊልሞች በፌስቲቫሉ ለእይታ እና ለውይይት ይቀርባሉ። በፌስቲቫሉ ሰብአዊ መብቶችን ማዕከል ያደረጉ አዳዲስ እና ከዚህ በፊት ለዕይታ የቀረቡ በዓለም አቀፍ መድረኮች ጭምር ተቀባይነትን ያተረፉ የሙሉ ጊዜ እና አጫጭር ፊልሞች እንዲሁም ዘጋቢ ፊልሞች ለዕይታ ይቀርባሉ፡፡

በአምስቱ ከተሞች የሚካሄደው ሁለተኛው የሰብአዊ መብቶች ፊልም ፌስቲቫል፡-

  • በአዳማ- ታኅሣሥ 7 ቀን 2015 ዓ.ም. በኦሊያድ ሲኒማ፣ 
  • በአዲስ አበባ- ታኅሣሥ 18 ቀን 2015 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ቴአትር እና ባህል አዳራሽ 
  • በባሕር ዳር- ታኅሣሥ 4 ቀን 2015 ዓ.ም. በሙሉ ዓለም የባህል ማዕከል፣ 
  • በሃዋሳ- ታኅሣሥ 14 ቀን 2015 ዓ.ም. ሌዊ ሲኒማ እንዲሁም፣
  • በጅግጅጋ- ታኅሣሥ 9 ቀን 2015 ዓ.ም. በኤምሲኤም ሆቴል የሚካሄድ ይሆናል፡፡

15 ፊልሞች ለእይታ የተሰናዱበትና በመዓዛ ወርቁ ፊልም ፕሮዳክሽንስ አስተባባሪነት የሚዘጋጀው ይህ ፌስቲቫል በሴቶችና ሕፃናት መብቶች፣ በስደተኞች፣ ፍልሰተኞች እና በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች መብቶች፤ በአካል ጉዳተኞች እና አረጋውያን መብቶች፣ በፍትሐዊ እና ሰብአዊ የሥራ ክፍፍል፣ ለአካለ መጠን ያልደረሱ ሕፃናት ጉልበት ብዝበዛ እና ጥቃት፣ እንዲሁም በማረሚያ ቤት የወጣት ጥፋተኞች የሰብአዊ መብቶች አያያዝ ላይ የሚያጠነጥኑ ፊልሞች ተካተውበታል፡፡ ፊልሞቹ በአማርኛ፣ አፋን ኦሮሞ፣ ሶማሊኛ እና ሲዳምኛ ቋንቋዎች የተሠሩ ወይም አጋዥ ጽሑፍ (subtitle) አካተዋል፡፡

ፌስቲቫሉን በይፋ ለማስጀመር በተካሄደው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር፤ በሀገራችን የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አሁን ላለበት አሳሳቢ የሚባል ደረጃ ለመድረሱ ዘርፈ ብዙ ምክንያቶች ቢኖሩም፤ ስለ ሰብአዊ መብቶች ያለው አነስተኛ ግንዛቤ በአሉታዊ መልኩ አስተዋዖ አድርጓል ብለዋል። አክለውም ኢሰመኮ በአምስት ዓመት ስትራቴጂክ እቅዱ ከለያቸው ቁልፍ የውጤት መስኮች መካከል በሀገር አቀፍ ደረጃ ውጤታማ የሰብአዊ መብቶች ትምህርት እንዲኖር ማስቻል ሲሆን የኪነጥበብ ዘርፉ የሰብአዊ መብቶችን ግንዛቤ ከማስፋፋት እና ከማስተማር አኳያ ከፍያለ ሚና ይጫወታል። ይህ የሰብአዊ መብቶች ዓመታዊ የፊልም ፌስቲቫል በሰብአዊ መብቶች ጉዳዮች ላይ ለመወያየት፣ ለመመማማር እና በሰብአዊ መብቶ መርሆች የታነጸ ትውልድን ለመቅረጽ ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል። 

የኢሰመኮ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ በበኩላቸው ኢሰመኮ “ሰብአዊ መብቶች ባሕል የሆኑባት ኢትዮጵያን ማየት” የሚለውን ራዕይ ለማሳካት የትምህርትና የስልጠና ተቋማት፣ ማኅበራዊ ሚዲያን ጨምሮ መገናኛ ብዙኃንና የኪነጥበብ ዘርፉ የሰብአዊ መብቶች ግንዛቤን ለማዳበር፣ የሰብአዊ መብቶች ሥራዎችን ለማስተዋወቅ እና ለማኅበረሰቡ ለማሰራጨት አስተዋጽዖ ያላቸው በመሆናቸው ትኩረት የሚሰጣቸው ናቸው ብለዋል።

በፌስቲቫሉ ላይ ጥሪ የተደረገላቸው በፊልም እና በሌሎች የኪነጥበብ ዘርፍ ሙያ ላይ የተሰማሩ ባለሙያዎች፣ የተለያዩ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ተወካዮች፣ በሰብአዊ መብቶች ላይ ትኩረታቸውን አድርገው የሚሠሩ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት፣ መገናኛ ብዙኀን፣ ተማሪዎች እና ሌሎች ተመልካቾች ይታደሙበታል፡፡

በፌስቲቫሉ የሚቀርቡ ፊልሞች ዝርዝር እዚህ ተያይዟል

Related posts

December 27, 2022August 28, 2023 2nd Film Festival
የኢሰመኮ ሁለተኛው ዓመታዊ የሰብአዊ መብቶች ፊልም ፌስቲቫል ተጠናቀቀ
November 30, 2021October 3, 2023 1st Film Festival
ኢሰመኮ እና ኢሰመድህ በኅዳር እና በታኅሣሥ ወራት 2014 ዓ.ም. ታስበው የሚውሉ ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ቀናትን በተለያዩ ዝግጅቶች ያከብራሉ
December 6, 2021October 3, 2023 1st Film Festival
ለመጀመሪያ ጊዜ የሚደረግ ዓመታዊ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ፊልም ፌስቲቫል በአዲስ አበባ፣ በአዳማ እና በሀዋሳ ከተሞች ይዘጋጃል
December 5, 2022August 28, 2023 2nd Film Festival
የመጀመሪያው የሰብአዊ መብቶች ፊልም ፌስቲቫል በጨረፍታ

Signup for the Latest Update from EHRC

Submit your email to singup
Facebook Like us on FacebookXFollow us on XYouTube Follow us on YouTubeLinkedin Follow us on LinkedinWhatsApp WhatsAppTikTok TikTokTelegram TelegramInstagram InstagramFlicker Flickr

Useful Links

  • NANHRI
  • GANHRI
  • OHCHR
  • ACHPR
  • TRANSITIONAL JUSTICE

Get Involved

  • Jobs
  • Events
  • Contact Us
  • Telegram Bot
  • Subscribe to our newsletter

Connect with Us

  • Facebook
  • Twitter
  • LinkedIn
  • YouTube
  • Flickr
  • Instagram
Descriptive Text

We are an independent
national human rights
institution tasked with
the promotion and protection of human
rights in Ethiopia.

Submit your email to get the latest update from EHRC

Address: Sunshine Tower No. 5, Meskel Square, on Bole Road next to Hyatt Regency Hotel, Addis Ababa, Ethiopia
Tel: +251115504031 | Fax: +251 11 550 4125 | PO Box 1165 Addis Ababa | Email: info@ehrc.org


The contents of this website, excepting third party content for which the Commission bears no responsibility,
may be freely used and copied for educational and other non-commercial purposes, provided that any such reproduction is accompanied by an acknowledgement of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC). Source of images used in the content of this website: EHRC Media and Communications Department Archive and Creative Common License.

This website is managed by the Media and Communications team of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC).

We are using cookies to give you the best experience on our website.

You can find out more about which cookies we are using or switch them off in .

Scroll to top
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
    • Addis Ababa
    • Afar
    • Amhara
    • Benishangul Gumuz
    • Central Ethiopia
    • Dire Dawa
    • Gambella
    • Harari
    • Oromia
    • Sidama
    • Somali
    • South Ethiopia
    • South West Ethiopia Peoples’
    • Tigray
  • Areas of Work
    • Economic, Social & Cultural Rights
    • Civil & Political Rights
    • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
    • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
    • Human Rights Monitoring & Investigation
    • Women’s & Children’s Rights
    • Human Rights Education
    • Human Rights Film Festival
    • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Search
Ethiopian Human Rights Commission - EHRC
Powered by  GDPR Cookie Compliance
Privacy Overview

This website uses cookies so that we can provide you with the best user experience possible. Cookie information is stored in your browser and performs functions such as recognising you when you return to our website and helping our team to understand which sections of the website you find most interesting and useful.

Strictly Necessary Cookies

Strictly Necessary Cookie should be enabled at all times so that we can save your preferences for cookie settings.

If you disable this cookie, we will not be able to save your preferences. This means that every time you visit this website you will need to enable or disable cookies again.