Skip to content
Facebook Twitter
Ethiopian Human Rights Commission – EHRC
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
        • Regions

          EHRC is an independent federal institution tasked with the promotion and protection of human rights in Ethiopia.

        • Addis Ababa
        • Afar
        • Amhara
        • Benishangul Gumuz
        • Gambella
        • Oromia
        • Somali
        • SNNP
        • Tigray
  • Areas of Work
        • Areas of Work

          We are an independent national human rights institution tasked with the promotion & protection of human rights in Ethiopia.

        • Economic, Social and Cultural Rights
        • Civil & Political Rights
        • IDPs, Refugees & Migrants Rights
        • Rights of Persons with Disabilities and the Rights of Older Persons
        • Women’s and Children’s Rights
        • HR Monitoring and Investigation
        • Human Rights Education
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • Events
  • Resources
 
Ethiopian Human Rights Commission – EHRCEthiopian Human Rights Commission – EHRC

በአፋር ክልል የሰመራ ጣብያ ሙሉ በሙሉ መዘጋትን በተመለከተ

September 15, 2022October 7, 2022 EHRC Quote

በሰመራ ጣቢያዎች ተይዘው የነበሩ ሰዎች በኢሰመኮ ምክረ ሃሳቦች መሰረት እንዲለቀቁና በፍላጎታቸው መሰረት ወደመጡባቸው አካባቢዎች እንዲመለሱ መደረጉ ኢሰመኮ በበጎ የሚመለከተው ነው

Twitter Facebook Telegram Email Whatsapp Print

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ሰኔ 22 ቀን 2014 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ በሚገኙ ሰመራ እና አጋቲና ካምፖች በመባል በሚታወቁ ቦታዎች ከትግራይ ክልል አዋሳኝ ከሆኑ 3 የአፋር ክልል ወረዳዎች በታኅሣሥ ወር 2014 ዓ.ም. ተይዘው የቆዩና በሁለቱ ካምፖች የሚገኙ ወደ 9 ሺህ የሚጠጉ የትግራይ ተወላጆች ያሉበትን አሳሳቢ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ በመግለጽ በአፋጣኝና ያለቅድመ ሁኔታ እንደለቀቁ ማሳሰቡ ይታወሳል።

ኢሰመኮ በሁለቱ ካምፖች ተይዘው የሚገኙ ሰዎች ችግር በሚፈታበት ሁኔታ ላይ በሐምሌ 6 ቀን 2014 ዓ.ም. በሰመራ ከተማ ከክልሉ መንግሥት ኃላፊዎች ጋር በተደረገው ምክክር የክልሉ የመንግሥት ኃላፊዎች ችግሩን ለመፍታት አስፈላጊውን እርምጃ እንደሚወስዱ በገለጹት መሰረት በክልሉ ከሚንቀሳቀሱ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በመተባበር የምግብ፣ ሕክምና እና መጠለያ አቅርቦትን ለማሻሻል እንዲሁም የመንቀሳቀስ ነፃነቶቻቸውን በተሻለ ሁኔታ ለማረጋገጥ ጥረቶች ተደርገዋል፤ እንዲሁም ምዝገባ እና በሁለቱም ካምፖች የሚገኙ ሰዎች ወደየትኛው አካባቢዎች መመለስ እንደሚፈልጉ ለማወቅ የፍላጎት ዳሰሳዎች ተከናውናዋል። በማስከተልም ነሐሴ 12 ቀን 2014 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ በእነዚህ ካምፖች የሚገኙ የትግራይ ተወላጆችን ወደ መኖሪያ ቀዬአቸው የመመለሱን ሂደት በበጎ የሚመለከተው እና ክትትል ማድረጉን የሚቀጥል መሆኑን ማስታወቁ የሚታወስ ነው።

በዚህ መሰረት በሰመራ መጠለያ ጣቢያ ውስጥ የነበሩ ሰዎች በዋናነት በአፋር ክልል አብአላ አካባቢ ወደሚገኙ የቀድሞ መኖሪያ አካባቢዎቻቸው የመመለስ ፍላጎት በማሳየታቸው ከነሐሴ 17 ቀን 2014 ዓ.ም. እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2014 ዓ.ም. በተከናወነ የመመለስ ሥራ ወደ መኖሪያ አካባቢዎቻቸው እንዲመለሱ ተደርጎ የሰመራ መጠለያ ጣቢያ እንዲዘጋ ሆኗል።  

በአጋቲና የመጠለያ ካምፕ ውስጥ የሚገኙ ወደ 600 የሚጠጉ የትግራይ ተወላጆች በተከናወነው የፍላጎት ዳሰሳ ወደ ትግራይ ክልል መሄድ የሚፈልጉ መሆኑን የገለጹ ቢሆንም በአፋር ክልል መንግሥት እና በትግራይ ክልል አስተዳደር መካከል ቀጥተኛ ግንኙነት ባለመኖሩ በዓለም አቀፍ ድርጅቶች በኩል ለማስፈጸም ጥረቶች በመደረግ ላይ ባሉበት ወቅት ጦርነቱ በድጋሚ በመቀስቀሱ ለማስፈጸም አስቸጋሪ ሁኔታ መፈጠሩን ኮሚሽኑ ተገንዝቧል። የኢሰመኮ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ የአፋር ክልላዊ መንግሥት በሰመራ እና አጋቲና መጠለያ ጣቢያዎች ተይዘው የነበሩ ሰዎች በኢሰመኮ ምክረ ሃሳቦች መሰረት እንዲለቀቁና በፍላጎታቸው መሰረት ወደመጡባቸው አካባቢዎች እንዲመለሱ በማድረጉ ኢሰመኮ እውቅና የሚሰጥ መሆኑን ገልጸው በተለይ በዚህ ሥራ ላይ በዋናነት የተሳተፉትን የአፋር የክልል አደጋ መከላከል እና የምግብ ዋስትና ቢሮ፣ የክልሉ የጤና ቢሮ፣ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን እንዲሁም በዚህ ሂደት ለክልሉ መንግሥት ድጋፍ ያደረጉ ዓለም አቀፍ ተቋማትን ኮሚሽኑ ለማመስገን ይወዳል ብለዋል። 

Location Afar

Related posts

June 8, 2022October 7, 2022 Human Rights Concept
Press Freedom and Pre-trial detention
June 18, 2022October 6, 2022 EHRC Quote
በማኅበራዊ መገናኛ ብዙኃን በመዘዋወር ላይ የሚገኘውን በርካታ ሰዎች ከመኪና እንዲወርዱ በማድረግ በጅምላ ሲገደሉ የሚያሳየውን ተንቀሳቃሽ ምስል
August 10, 2022October 5, 2022 Human Rights Concept
The Right to Freedom of Movement of IDPs
November 24, 2020February 11, 2023 Report
በትግራይ ክልል፣ አክሱም ከተማ የተፈጸመው ከፍተኛ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ምርመራ የመጀመሪያ ደረጃ (ቀዳሚ) ሪፖርት

Signup for the Latest Update from EHRC

Submit your email to singup
Facebook Like us on FacebookTwitter Follow us on Twitter

Useful Links

  • NANHRI
  • GANHRI
  • OHCHR
  • ACHPR

Get Involved

  • Jobs
  • Events
  • Contact Us
  • Telegram Bot

Connect with Us

  • Facebook
  • Twitter
  • LinkedIn
  • YouTube
EHRC
We are an independent national human rights
institution tasked with the promotion & protection of
human rights in Ethiopia
Submit your email to get the latest update from EHRC

Address: Sunshine Tower No. 5, Meskel Square, on Bole Road next to Hyatt Regency Hotel, Addis Ababa, Ethiopia
Tel: +251115504031 | Fax: +251 11 550 4125 | PO Box 1165 Addis Ababa | Email: info@ehrc.org

© 2023 Copyright Ethiopian Human Rights Commission (EHRC). All Rights Reserved. Powered by 360Ground

We are using cookies to give you the best experience on our website.

You can find out more about which cookies we are using or switch them off in settings.

Scroll to top
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
    • Addis Ababa
    • Afar
    • Amhara
    • Benishangul Gumuz
    • Gambella
    • Oromia
    • Somali
    • SNNP
    • Tigray
  • Areas of Work
    • Economic, Social and Cultural Rights
    • Civil & Political Rights
    • IDPs, Refugees & Migrants Rights
    • Rights of Persons with Disabilities and the Rights of Older Persons
    • Women’s and Children’s Rights
    • HR Monitoring and Investigation
    • Human Rights Education
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Videos
    • Newsletters
    • Events
  • Resources
Facebook Twitter
Search
Ethiopian Human Rights Commission - EHRC
Powered by  GDPR Cookie Compliance
Privacy Overview

This website uses cookies so that we can provide you with the best user experience possible. Cookie information is stored in your browser and performs functions such as recognising you when you return to our website and helping our team to understand which sections of the website you find most interesting and useful.

Strictly Necessary Cookies

Strictly Necessary Cookie should be enabled at all times so that we can save your preferences for cookie settings.

If you disable this cookie, we will not be able to save your preferences. This means that every time you visit this website you will need to enable or disable cookies again.