Skip to content
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Ethiopian Human Rights Commission – EHRC
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
        • Regions

          EHRC is an independent federal institution tasked with the promotion and protection of human rights in Ethiopia.

        • Addis Ababa
        • Afar
        • Amhara
        • Benishangul Gumuz
        • Gambella
        • Oromia
        • Somali
        • Tigray
        • Central Ethiopia
        • Dire Dawa
        • Harari
        • Sidama
        • South Ethiopia
        • South West Ethiopia Peoples'
  • Areas of Work
        • Areas of Work

          We are an independent national human rights institution tasked with the promotion & protection of human rights in Ethiopia.

        • Economic, Social & Cultural Rights
        • Civil & Political Rights
        • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
        • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
        • Women’s & Children’s Rights
        • Human Rights Education
        • Human Rights Monitoring & Investigation
        • Human Rights Film Festival
        • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
 
Ethiopian Human Rights Commission – EHRCEthiopian Human Rights Commission – EHRC

በግንባታ የሥራ ዘርፍ ደኅንነቱ የተጠበቀ እና ጤናማ የሥራ ሁኔታን ለማረጋገጥ የሕግና ፖሊሲ አተገባበሮችን ማሻሻል ያስፈልጋል

July 7, 2023August 28, 2023 Press Release, Report

በሥራ ዘርፉ የሚንቀሳቀሱ አስፈጻሚ ተቋማትን በማጠናከር፣ ባለድርሻዎችን አቀናጅቶ እና አስተባብሮ የሚመራ ሥርዓት መዘርጋት አለበት

Twitter Facebook Telegram Email Whatsapp Download Download Print

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ደኅንነቱ የተጠበቀ እና ጤናማ የሥራ ሁኔታ መብትን በተመለከተ የግንባታ ሥራ ዘርፍ ላይ ያተኮረ ባለ 36 ገጽ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ክትትል ሪፖርት ዛሬ ይፋ አድርጓል።

ደኅንነቱ እና ጤንነቱ የተጠበቀ የሥራ ሁኔታ የማግኘት መብት ያለምንም መድልዎ በማንኛውም የሥራ ዘርፍ እና የቅጥር ዓይነት ለሚሠሩ ሠራተኞች የተሰጠ መብት ሲሆን፣ ከፍትሐዊ እና ምቹ የሥራ ሁኔታዎች መብት መሠረታዊ ክፍሎች መካከል አንዱ እና ከሌሎች መብቶች በተለይም ከአካላዊ እና አእምሯዊ ጤና መብት ጋር የተቆራኘ ነው። የግንባታ ኢንዱስትሪ ከፍተኛ የሥራ ላይ አደጋዎች የሚከሰቱበት እና ለደኅንነት እና ለጤንነት አስጊ ከሆኑ ዘርፎች መካከል በመሆኑ፣ ደኅንነቱ የተጠበቀ እና ጤናማ የሥራ ሁኔታ መብት ላይ ሀገር አቀፍ የሕግና ፖሊሲ ማዕቀፎችን እና አተገባበራቸውን ለመፈተሽ ጥሩ ማሳያ ነው።

ሪፖርቱን ለማዘጋጀት በአጠቃላይ ከ182 ሰዎች መረጃ፣ ሰነዶች እና ማስረጃዎች የተሰበሰቡ ሲሆን፣ 44 ከሚመለከታቸው የመንግሥት ቢሮዎች፣ 33 ከሕንጻ ተቋራጮች፣ 72 የግንባታ ሠራተኞች እና 10 ጉዳዩ ከሚመለከታቸው መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት ተሳተፈዋል። በተጨማሪም በጉዳዩ ላይ በተዘጋጀ የውይይት መድረክ የተለያዩ ተቋማትን እና ባለድርሻዎችን የወከሉ 23 ተሳታፊዎች ተካተዋል፡፡ ክትትሉ በአዳማ፣ በአዲስ አበባ፣ በባሕር ዳር፣ በሃዋሳ እና በጅግጅጋ ከተሞች የተደረገ ነው።

በሁሉም የሥራ ዘርፎች ተፈጻሚ መሆን ካለባቸው ዓለም አቀፍ እና አህጉራዊ ጤናማ እና ደኅንነቱ የተጠበቀ የሥራ ሁኔታ/ከባቢ ከማግኘት መብት በተጨማሪ፣ በተለይ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለግንባታ ሥራ ዘርፉ በአዋጅ እና በመመሪያ ደረጃ የተደነገጉ እና መንግሥታዊ ተቋማትም ሆነ እና ቀጣሪዎች (የግንባታ ተቋራጮች) ሊተገብሯቸው የሚገቡ መስፈርቶች እና መመሪያዎች አሉ። ሆኖም በአስፈጻሚ አካላት ጭምር ያለው የግንዛቤ እጥረት ይህም የፈጠረው ሕጉን ለማስፈጸም እና ለማረጋገጥ የሚወሰዱ እርምጃዎች ዝቅተኛ መሆን ለእነዚህ መስፈርቶች አለመከበር ዋነኛው ምክንያት መሆኑን ክትትሉ አረጋግጧል። ለምሳሌ ለሴት ሠራተኞች ከባድ ወይም ለጤና ጎጂ የሆኑ ወይም የመውለድ ሁኔታን የሚያውኩ ሥራዎችን የተመለከቱ ድንጋጌዎች፣ በተለይም የሴት ሠራተኞችን ጉልበት በመጠቀም የሚካሄድ ማናቸውም ክብደትን ከቦታ ቦታ የማንቀሳቀስ፣ የመሸከም፣ የማጓጓዝ፣ የማንሳት፣ የማውረድ፣ የማውጣት፣ የመጎተት፣ የመሳብና የመሳሰሉት ሥራዎች፣ የክብደት መጠን ጣሪያ እና የመሳሰሉት በአብዛኛው ክትትል በተደረገባቸው የግንባታ ሥራዎች ሲጣስ አልያም በተሟላ መልኩ አለመተግበሩ ተመልክቷል።

በተጨማሪም ደኅንነቱ የተጠበቀ እና ጤናማ የሥራ ከባቢ ከማግኘት መብት የተመለከቱ ድንጋጌዎችን የመተግበር ኃላፊነት ያለባቸው ተቋማት ተቋማዊ ችግሮች፤ ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላትን አስተባብሮ እና አቀናጅቶ የሚመራ ጠንካራ ሥርዓት አለመኖር፤ ደካማ የመረጃ አያያዝ እና የአጠቃቀም ሥርዓት፤ የግንባታ ግዢ ጨረታዎች ዝቅተኛ ዋጋን መሠረት ያደረጉ መሆናቸው እና ሠራተኞች ሊያጋጥሟቸው የሚችሉ በሂደት የሚገለጡ የጤና መጓደሎች እና በሽታዎች ችላ የተባሉ መሆናቸው መሻሻል ከሚገባቸው ክፍተቶች መካከል ተጠቅሰዋል፡፡

በግንባታ ሥራ ዘርፍ ደኅንነቱ የተጠበቀ እና ጤናማ የሥራ ሁኔታ መብት በተሻለ ሁኔታ እንዲተገበር እና ከላይ የተዘረዘሩትን ተግዳሮቶች ለመቅረፍ ይረዳሉ በማለት ከተለዩ የአሠራር፣ የፖሊሲ እና የሕግ ማሻሻያ ምክረ ሐሳቦች መካከል ሕጎችን ማስተዋወቅ እና የመብቱን ተፈጻሚነት ለማረጋገጥ የሚረዱ ሥርዓቶችን መዘርጋት እንዲሁም የሙያ ደኅንነት እና ከጤንነት ጋር ተያያዥነት ያላቸውን የዓለም አቀፍ የሥራ ድርጅት ስምምነቶችን በማጽደቅ ሥራ ላይ ማዋል የሚሉት ይገኙበታል።

የኢሰመኮ የሲቪል፣ የፖለቲካ እና ማኅበራዊ-ኢኮኖሚያዊ መብቶች ኮሚሽነር ዶ/ር አብዲ ጅብሪል “በግንባታ ሥራ ዘርፍ ደኅንነቱ የተጠበቀ እና ጤናማ የሥራ ሁኔታ መብትን ለማረጋገጥ ጉዳዩ የሚመለከታቸውን አካላት አስተባብሮ እና አቀናጅቶ የሚመራ ጠንካራ ሥርዓት መዘርጋት ያስፈልጋል” ብለዋል። አክለውም “ሕጎችን ከማርቀቅ ተፈጻሚነታቸውን እስከ ማረጋገጥ ባለው ሂደት ውስጥ ሁሉም የሚመለከታቸው ተቋማት በመናበብ እና በትብብር መሥራት አለባቸው” ብለዋል።

ሙሉ ሪፖርቱ እዚህ ተያይዘዋል
አንኳር ጉዳዮች

Related posts

October 12, 2023August 8, 2024 Event Update
ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ፡- የጤና መብት እና የግንባታ ዘርፍ ደኅንነቱ የተጠበቀና ጤናማ የሥራ ሁኔታ መብት አተገባበር ክትትል ሪፖርቶችን መሠረት ያደረጉ የውትወታ መድረኮች ተካሄዱ
June 13, 2023August 28, 2023 Event Update
በግንባታ ዘርፍ ደኅንነቱ የተጠበቀ እና ጤናማ የሥራ ሁኔታ መብት አተገባበር
February 16, 2022August 28, 2023 Human Rights Concept
ውሃ የማግኘት ሰብአዊ መብት
October 18, 2023October 23, 2023 Event Update
በምግብ ሥርዓት፣ ምግብ የማግኘት መብት እና ሰብአዊ መብትን መሠረት ያደረገ አቀራረብ ዙሪያ የተካሄዱ ስልጠናዎች

Signup for the Latest Update from EHRC

Submit your email to singup
Facebook Like us on FacebookXFollow us on XYouTube Follow us on YouTubeLinkedin Follow us on LinkedinWhatsApp WhatsAppTikTok TikTokTelegram TelegramInstagram InstagramFlicker Flickr

Useful Links

  • NANHRI
  • GANHRI
  • OHCHR
  • ACHPR
  • TRANSITIONAL JUSTICE

Get Involved

  • Jobs
  • Events
  • Contact Us
  • Telegram Bot
  • Subscribe to our newsletter

Connect with Us

  • Facebook
  • Twitter
  • LinkedIn
  • YouTube
  • Flickr
  • Instagram
Descriptive Text

We are an independent
national human rights
institution tasked with
the promotion and protection of human
rights in Ethiopia.

Submit your email to get the latest update from EHRC

Address: Sunshine Tower No. 5, Meskel Square, on Bole Road next to Hyatt Regency Hotel, Addis Ababa, Ethiopia
Tel: +251115504031 | Fax: +251 11 550 4125 | PO Box 1165 Addis Ababa | Email: info@ehrc.org


The contents of this website, excepting third party content for which the Commission bears no responsibility,
may be freely used and copied for educational and other non-commercial purposes, provided that any such reproduction is accompanied by an acknowledgement of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC). Source of images used in the content of this website: EHRC Media and Communications Department Archive and Creative Common License.

This website is managed by the Media and Communications team of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC).

We are using cookies to give you the best experience on our website.

You can find out more about which cookies we are using or switch them off in .

Scroll to top
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
    • Addis Ababa
    • Afar
    • Amhara
    • Benishangul Gumuz
    • Central Ethiopia
    • Dire Dawa
    • Gambella
    • Harari
    • Oromia
    • Sidama
    • Somali
    • South Ethiopia
    • South West Ethiopia Peoples’
    • Tigray
  • Areas of Work
    • Economic, Social & Cultural Rights
    • Civil & Political Rights
    • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
    • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
    • Human Rights Monitoring & Investigation
    • Women’s & Children’s Rights
    • Human Rights Education
    • Human Rights Film Festival
    • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Search
Ethiopian Human Rights Commission - EHRC
Powered by  GDPR Cookie Compliance
Privacy Overview

This website uses cookies so that we can provide you with the best user experience possible. Cookie information is stored in your browser and performs functions such as recognising you when you return to our website and helping our team to understand which sections of the website you find most interesting and useful.

Strictly Necessary Cookies

Strictly Necessary Cookie should be enabled at all times so that we can save your preferences for cookie settings.

If you disable this cookie, we will not be able to save your preferences. This means that every time you visit this website you will need to enable or disable cookies again.