የሕፃናት መብቶች ስምምነት፣ አንቀጽ 20 (1) እና (2)

  • ለጊዜው ወይም ለዘለቄታው ከቤተሰቡ የተለየ ወይም ለራሱ ጥቅም ሲባል ከቤተሰቡ ጋር እንዲቆይ ሊደረግ የማይችል ሕፃን የመንግሥትን ልዩ ጥበቃ እና ድጋፍ የማግኘት መብት አለው።
  • አባል ሀገራት በብሔራዊ ሕጎቻቸው መሠረት ከቤተሰቡ የተለየ ሕፃን አማራጭ እንክብካቤ ማግኘቱን ማረጋገጥ ይገባቸዋል።

የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት፣ አንቀጽ 36 (5)

  • መንግሥት ለእጓለ ማውታን ልዩ ጥበቃ ያደርግላቸዋል። በጉዲፈቻ የሚያድጉበትን ሥርዓት የሚያመቻቹና የሚያስፋፉ እንዲሁም ደኅንነታቸውንና ትምህርታቸውን የሚያራምዱ ተቋሞች እንዲመሠረቱ ያበረታታል።