Skip to content
Facebook Twitter
Ethiopian Human Rights Commission – EHRC
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
        • Regions

          EHRC is an independent federal institution tasked with the promotion and protection of human rights in Ethiopia.

        • Addis Ababa
        • Afar
        • Amhara
        • Benishangul Gumuz
        • Gambella
        • Oromia
        • Somali
        • SNNP
        • Tigray
  • Areas of Work
        • Areas of Work

          We are an independent national human rights institution tasked with the promotion & protection of human rights in Ethiopia.

        • Economic, Social and Cultural Rights
        • Civil & Political Rights
        • IDPs, Refugees & Migrants Rights
        • Rights of Persons with Disabilities and the Rights of Older Persons
        • Women’s and Children’s Rights
        • HR Monitoring and Investigation
        • Human Rights Education
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • Events
  • Resources
 
Ethiopian Human Rights Commission – EHRCEthiopian Human Rights Commission – EHRC

አፋር ክልል: የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች እና ተመላሾች በዘላቂነት እንዳይቋቋሙ ተግዳሮት ከሆነው የኢኮኖሚ እና የንግድ እንቅስቃሴ ገደብ ጋር የተገናኙ ችግሮች ሊቀረፉ ይገባል

February 22, 2023February 22, 2023 Press Release

መንግሥት በአፋር ክልል በዞን ሁለት፣ በዞን አራት እንዲሁም በሰመራ ከተማ ለሚገኙ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች እና ተመላሾች በቂ፣ ወቅቱን የጠበቀ እና ተደራሽ የሆነ የሰብአዊ ድጋፍ የማቅረብ ኃላፊነቱን በተገቢው መንገድ መወጣት አለበት

Twitter Facebook Telegram Email Whatsapp Print

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በአፋር ክልል በዞን ሁለት (ኪልበቲ ረሱ)፣ በረሐሌ፣ አብአላ እና መጋሌ ወረዳዎች በሚገኙ በ6 መጠለያ ጣቢያዎች፤ በሰመራ ከተማ በሰመራ ስታዲየም ውስጥ የሚኖሩ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች እንዲሁም በዞን አራት (ፈንቲ ረሱ) በጉሊና፣ ያሎ ወረዳዎች እና በዞን ሁለት አብአላ ወረዳ ጉቤ ቀበሌ የሚገኙ ተመላሾች የሰብአዊ መብቶች አያያዝ ሁኔታ ላይ ከኅዳር 10 ቀን 2015 ዓ.ም. እስከ ታኅሣሥ 1 ቀን 2015 ዓ.ም. ክትትል አከናውኗል።

የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች በመፈናቀል ሂደት የቤተሰብ አባሎች ሞት፣ አካል ጉዳት እና ድብደባን ጨምሮ የተለያዩ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት የደረሰባቸው መሆኑን፤ ቤቶቻቸው፣ ንብረቶቻቸው እና ከብቶቻቸው መውደማቸውንና መዘረፋቸውን ለኮሚሽኑ አስረድተዋል። የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ምዝገባ እና ሰነድን በሚመለከት፤ ሰዎች ከመፈናቀላቸው በፊት በቀበሌው የሚገኘውን የነዋሪ ብዛት መጠን በቤተሰብ ደረጃ መረጃ ከመያዝ ባሻገር በመጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ ለሚኖሩ ተፈናቃዮች እና ተመላሾች ምዝገባ እንዳልተከናወነ እና የወሳኝ ኩነት ምዝገባን ጨምሮ ሌሎች ሰነዶችን የመስጠት አገልግሎት አለመጀመሩን ኮሚሽኑ በክትትሉ ለማወቅ ችሏል፡፡

በተጨማሪም በትግራይ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች የሚኖሩ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ዳግም ግጭት ሊከሰት ይችላል የሚል ሥጋት እንዳለባቸው የገለጹ ሲሆን፤ የጦርነት ቀጠና የነበሩ እንደ ጉሊና ወረዳ ፎኪሳ ቀበሌ ባሉ አካባቢዎች ፈንጂ እና መሰል የጦር መሣሪያዎችን በማምከን አካባቢውን ከአደገኛ የጦር መሳሪያዎች የማጽዳት ሥራ በአግባቡ ባለመከናወኑ በተመላሾች ላይ የደኅንነት ሥጋት ፈጥሮባቸዋል፡፡

ክትትል በተደረገባቸው አካባቢዎች ተመላሾች በራሳቸው ሙሉ ፈቃድ የተመለሱ ቢሆንም፤ መደበኛ ኑሯቸውን ለመቀጠል የሚያስችላቸውን ምቹ ሁኔታ በመፍጠር ለተፈናቃዮች ዘላቂ መፍትሔ ማፈላለግን በተመለከተ ክፍተቶች እንዳሉ የኮሚሽኑ ክትትል ያመላክታል፡፡ ከሰሜኑ ጦርነት ጋር በተያያዘ ከሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች በአፋር ክልል ዞን ሁለት እና ዞን አራት በኩል በየብስ ትራንስፖርት ወደ ትግራይ ክልል ተጓጉዘው ይገቡ የነበሩ ነዳጅን ጨምሮ የተለያዩ መሠረታዊ የፍጆታ ዕቃዎች እንዳይገቡ የተጣለው እገዳ ባለመነሳቱ በሁለቱ ዞኖች ውስጥ የሚደረገውን የንግድ እንቅስቃሴ ከመገደቡ በተጨማሪ በፍጆታ ዕቃዎች ላይ ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ አስከትሏል። ይህም በአካባቢው ለተደጋጋሚ መፈናቀል የተዳረጉ ነዋሪዎች በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ሲካሄድ የቆየው ግጭት ካስከተለባቸው የሰብአዊ ቀውስ በተጨማሪ በቂ እና ወቅቱን የጠበቀ የሰብአዊ ድጋፍ ካለመቅረቡ በተጨማሪ የንግድ እንቅስቃሴው ገደብ ባለመነሳቱ ምክንያት እየደረሰባቸው ያለው ያልተገባ ኢኮኖሚያዊ ጫና፤ ተፈናቃዮች እና ተመላሾች በዘላቂነት እንዲቋቋሙ አስቻይ ሁኔታዎች እንዳይፈጠር ተግዳሮት ሆኗል።

ኢሰመኮ ባከናወነው ክትትል የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችና ተመላሾች በቂ፣ ወቅቱን የጠበቀ እና ተደራሽ የሆነ ምግብ፣ ውሃ፣ መጠለያ፣ የጤና አገልግሎት፣ ትምህርት እና ሌሎች ማኅበራዊ አገልግሎቶችን ያካተተ የሰብአዊ ድጋፍ እየቀረበላቸው እንዳልሆነ ተመልክቷል፡፡ በተለይ በጦርነቱ ወቅት የሕክምና ቁሳቁሶች፣ የመድኃኒቶች እና የክትባት ማስቀመጫ ፍሪጅን ጨምሮ በርካታ የጤና አገልግሎት ተቋማት በመዘረፋቸውና በመውደማቸው የሕክምና ቁሳቁስ እና መድኃኒት እጥረት ፈጥሯል። በተመሳሳይ ልዩ ጥበቃ እና ድጋፍ ለሚሹ ተፈናቃዮች ማለትም ለሚያጠቡ እናቶች፣ ነፍሰጡሮች፣ ሕፃናት፣ አካል ጉዳተኞች፣ አረጋውያን እና ተጓዳኝ ሕመም ላለባቸው ተፈናቃዮች የመብቶች ጥሰት ተጋላጭነታቸውን እና ልዩ ፍላጎታቸውን መሠረት ያደረገ የሰብአዊ ድጋፍ እንደማይቀርብ፣ ለሕፃናት እና አጥቢ እናቶች የሚሰጥ የተለየ የምግብ ድጋፍ ስለሌለ ለምግብ እጥረት የተጋለጡ መኖራቸውን ኮሚሸኑ ባደረገው ክትትል ተገንዝቧል፡፡

ኮሚሽኑ ክትትል በተደረገባቸው አካባቢዎች የነበረውን አሳሳቢ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ከለየ በኋላ ጉዳዩ ለሚመለከታቸው የፌዴራል እና የክልል መንግሥት ተቋማት የሁኔታውን አሳሳቢነት የሚገልጽ በተለይ የሰብአዊ ድጋፍ አቅርቦትን እና የዘላቂ መፍትሔ ማፈላለግን በተመለከተ የተስተዋሉ ክፍተቶች እንዲታረሙ በቃል እና በጽሑፍ ምክረ ሐሳቦችን በማጋራት ሁኔታው እንዲሻሻል ሲወተውት ቆይቷል፡፡ በዚህ መሠረት በኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን እንዲሁም በአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት አደጋ ሥጋት አመራርና የምግብ ዋስትና ኮሚሽን አስተባባሪነት ክትትሉ በተደረገባቸው አካባቢዎች ለሚኖሩ ተፈናቃዮች ምግብ እና ምግብ-ነክ ያልሆኑ የሰብአዊ ድጋፎች እንደቀረቡ ለኮሚሽኑ ገልጸዋል፡፡ ይሁንና ኢሰመኮ በድጋሚ ባደረገው ማጣራት ለተፈናቃዮች የተሰራጩ የሰብአዊ ድጋፎች በቂ፣ ወቅቱን የጠበቀ እና ተደራሽ ባለመሆናቸው በተፈናቃዮች ሁኔታ ላይ ተጨባጭ መሻሻል አለመኖሩን ለማወቅ ተችሏል፡፡

የኢሰመኮ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ “በክልሉ የሚገኙ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች የሰሜኑ ጦርነት ካስከተለባቸው የሰብአዊ ቀውስ በአግባቡ ለማገገም እና እራሳቸውን ችለው ለመኖር በሚያደርጉት ጥረት የንግድ እንቅስቃሴ ገደቡ አለመነሳቱ ተጨማሪ የኢኮኖሚ ጫና እየፈጠረባቸው እና መደበኛ ኑሯቸውን እንዳይቀጥሉ ከማድረጉ ባሻገር በዘላቂነት እንዳይቋቋሙ እንቅፋት ሆኗል” ሲሉ በአጽንዖት ገልጸዋል። አክለውም “የፌዴራል እና የክልሉ መንግሥታት እንደአስፈላጊነቱ ለጋሽ ድርጅቶችን በማስተባበር እየተሰጠ ያለውን ሰብአዊ ድጋፍ በማጠናከር ልዩ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው ተፈናቃዮችን ታሳቢ ያደረገ የሰብአዊ ድጋፍ እንዲቀርብ፤ እንዲሁም በክልሉ የሚገኙ ተፈናቃዮችን በዘላቂነት ለማቋቋም የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች እንዲፈጠሩ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሊረባረቡ ይገባል” ሲሉ አሳስበዋል።

Location Afar

Related posts

February 6, 2023February 6, 2023 Press Release
በደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ክልል በሚካሄደው ሕዝበ ውሳኔ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ክትትል የሚያደርግ የባለሙያዎች ቡድን ኢሰመኮ አሰማራ
February 25, 2022February 12, 2023 Event Update
የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችን አስመልክቶ የተለያዩ የመንግስት ተቋማት ሥልጣንና ኃላፊነት መለየት እና ቅንጅታዊ አሰራርን ማጠናከር
March 15, 2022February 14, 2023 Event Update
ኢሰመኮ 400ሺ ስደተኞች የሚገኙባቸውን 10 ጣቢያዎችን በመጎብኘት ለባለድርሻ አካላት የክትትል ሪፖርት አቀረበ
June 7, 2021February 12, 2023 Report
ብዛት ያላቸው ተፈናቃዮች ከግንቦት 16 ቀን 2013 ጀምሮ በጸጥታ ኃይሎች ተይዘዋል

Signup for the Latest Update from EHRC

Submit your email to singup
Facebook Like us on FacebookTwitter Follow us on Twitter

Useful Links

  • NANHRI
  • GANHRI
  • OHCHR
  • ACHPR

Get Involved

  • Jobs
  • Events
  • Contact Us
  • Telegram Bot

Connect with Us

  • Facebook
  • Twitter
  • LinkedIn
  • YouTube
EHRC
We are an independent national human rights
institution tasked with the promotion & protection of
human rights in Ethiopia
Submit your email to get the latest update from EHRC

Address: Sunshine Tower No. 5, Meskel Square, on Bole Road next to Hyatt Regency Hotel, Addis Ababa, Ethiopia
Tel: +251115504031 | Fax: +251 11 550 4125 | PO Box 1165 Addis Ababa | Email: info@ehrc.org

© 2023 Copyright Ethiopian Human Rights Commission (EHRC). All Rights Reserved. Powered by 360Ground

We are using cookies to give you the best experience on our website.

You can find out more about which cookies we are using or switch them off in settings.

Scroll to top
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
    • Addis Ababa
    • Afar
    • Amhara
    • Benishangul Gumuz
    • Gambella
    • Oromia
    • Somali
    • SNNP
    • Tigray
  • Areas of Work
    • Economic, Social and Cultural Rights
    • Civil & Political Rights
    • IDPs, Refugees & Migrants Rights
    • Rights of Persons with Disabilities and the Rights of Older Persons
    • Women’s and Children’s Rights
    • HR Monitoring and Investigation
    • Human Rights Education
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Videos
    • Newsletters
    • Events
  • Resources
Facebook Twitter
Search
Ethiopian Human Rights Commission - EHRC
Powered by  GDPR Cookie Compliance
Privacy Overview

This website uses cookies so that we can provide you with the best user experience possible. Cookie information is stored in your browser and performs functions such as recognising you when you return to our website and helping our team to understand which sections of the website you find most interesting and useful.

Strictly Necessary Cookies

Strictly Necessary Cookie should be enabled at all times so that we can save your preferences for cookie settings.

If you disable this cookie, we will not be able to save your preferences. This means that every time you visit this website you will need to enable or disable cookies again.