የአፍሪካ የሰዎች እና ሕዝቦች መብቶች ቻርተር የአረጋውያን መብቶች ፕሮቶኮል፣ አንቀጽ 9 

አባል ሀገራት፦ 

  • አረጋውያን ሴቶች ከጥቃት፣ ከወሲባዊ ጥቃት እንዲሁም በጾታ ላይ ከተመሠረተ መድልዎ መጠበቃቸውን ማረጋገጥ፤
  • አረጋውያን ሴቶች ከንብረት እና መሬት መብቶች ጋር ከተያያዙ በደሎች መጠበቃቸውን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ሕጎችን ማውጣት እና ሌሎች እርምጃዎችን መውሰድ፤ እንዲሁም
  • የአረጋውያን ሴቶችን የውርስ መብት ለመጠበቅ ተገቢውን ሕግ ማውጣት አለባቸው።