Skip to content
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Ethiopian Human Rights Commission – EHRC
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
        • Regions

          EHRC is an independent federal institution tasked with the promotion and protection of human rights in Ethiopia.

        • Addis Ababa
        • Afar
        • Amhara
        • Benishangul Gumuz
        • Gambella
        • Oromia
        • Somali
        • Tigray
        • Central Ethiopia
        • Dire Dawa
        • Harari
        • Sidama
        • South Ethiopia
        • South West Ethiopia Peoples'
  • Areas of Work
        • Areas of Work

          We are an independent national human rights institution tasked with the promotion & protection of human rights in Ethiopia.

        • Economic, Social & Cultural Rights
        • Civil & Political Rights
        • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
        • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
        • Women’s & Children’s Rights
        • Human Rights Education
        • Human Rights Monitoring & Investigation
        • Human Rights Film Festival
        • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
 
Ethiopian Human Rights Commission – EHRCEthiopian Human Rights Commission – EHRC

ኢሰመኮ ለመጀመሪያ ጊዜ ያዘጋጀውን የማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መብቶች ሁኔታ ዓመታዊ ሪፖርት ይፋ አደረገ

September 15, 2023September 15, 2023 Press Release, Report

ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ መብቶች ዘርፍ በ2016 ዓ.ም. የተሻለ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ዘርፍ ሲሆን፤ የፖሊሲና የሕግ ማሻሻያን ጨምሮ ጠንካራ የክትትልና የድጋፍ ሥርዓት መዘርጋት ያስፈልጋል

Twitter Facebook Telegram Email Whatsapp Download Download Print

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መብቶችን ሁኔታ የተመለከተ ዓመታዊ ባለ 29 ገጽ ሪፖርት ዛሬ ይፋ አድርጓል፡፡ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ የተዘጋጀው የዘርፍ ሪፖርት ኢሰመኮ ሐምሌ 5 ቀን 2015 ዓ.ም. ይፋ ካደረገው የኢትዮጵያ ዓመታዊ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ሪፖርት ላይ በተጨማሪነት ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መብቶች ላይ በማተኮር የታዩ መልካም እመርታዎች፣ ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡ አሳሳቢ ጉዳዮች እና ምክረ ሐሳቦችን አካቷል። 

ሪፖርቱ ከሰኔ ወር 2014 ዓ.ም. እስከ ሰኔ ወር 2015 ዓ.ም. ያለውን ጊዜ የሚሸፍን ሲሆን ኮሚሽኑ በማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መብቶች ዘርፍ በበጀት ዓመቱ ካከናወናቸው የሰብአዊ መብቶች ክትትልና ምርመራዎች፣ ጥናቶች፣ የውትወታ ሥራዎች፣ በግለሰቦች ከቀረቡ አቤቱታዎች፣ ከልዩ ልዩ የምክክር መድረኮች ላይ የተገኙ ግብአቶችን እና ሌሎች የመረጃ ምንጮችን በማጠናቀር የተዘጋጀ ነው።

በሪፖርት ዘመኑ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትራንስፖርት ቢሮ በባለሦስት እና አራት እግር አነስተኛ የሕዝብ ማመላለሻ አገልግሎት ተሽከርካሪዎች (ባጃጅ) ላይ ያሳለፈውን የእገዳ ውሳኔ ተከትሎ የኢሰመኮን ምክረ ሐሳቦች በመቀበል ለጉዳዩ እልባት መሰጠቱ፣ በኦሮሚያ እና በሶማሊ ክልሎች በሚገኙ የተለያዩ ዞኖች የተከሰተውን ድርቅ አስመልክቶ በተደረገው የሰብአዊ መብቶች ክትትል ሪፖርት በኮሚሽኑ የተሰጡ ምክረ ሐሳቦች አፈጻጸም ላይ በተለይም የዘላቂ መፍትሔ ፕሮጀክቶች አፈጻጸምን በተመለከተ አበረታች ሥራዎች መከናወናቸው እና የግል ሥራ እና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲ ሠራተኞች መብቶች አተገባበር እየተሻሻለ መምጣቱ በመልካም እመርታነት በሪፖርቱ ተካተዋል። በተጨማሪም በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል በተካሄደው ጦርነት ሳቢያ ጉዳት የደረሰባቸውን መሠረተ ልማቶችን መልሶ ለማቋቋም በፌዴራል መንግሥት ይፋ የተደረገው “የመልሶ ማቋቋምና ግንባታ ፕሮግራም” እና እነዚህን ተቋማት ወደ ነበሩበት ለመመለስ እየተደረጉ ያሉ እንቅስቃሴዎችም ተጠቃሽ ናቸው።

በሌላ በኩል፣ በሀገሪቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ የመጣው የጸጥታ ችግር እና እየናረ የመጣው የኑሮ ውድነትና የዋጋ ግሽበት፣ ሊደረስበት የሚችል ከፍተኛ አካላዊና አእምሯዊ ጤና የማግኘት፣ ትምህርት እና መጠለያ የማግኘት፣ የመሥራት፣ ከሚኖሩበት ቦታ ያላግባብ በኃይል ያለመፈናቀል እና ንብረት የማፍራት መብቶችን ጨምሮ ሌሎች የሰብአዊ መብቶች ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ማሳደራቸው በአሳሳቢነት ከተለዩ ጉዳዮች መካከል ናቸው። 

በአማራ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች ከሚያዝያ ወር 2015 ዓ.ም. ጀምሮ የተከሰቱ ግጭቶችና አለመረጋጋቶች በሰው ሕይወት እና ንብረት ላይ ጉዳት ከማድረሳቸውም በላይ ወቅቱ የግብርና ሥራ ቅድመ ዝግጅት የሚደረግበት የነበረ በመሆኑ አርሶ አደሩ ተረጋግቶ የግብርና ሥራውን እንዳይሠራ እና መደበኛ ሕይወቱን እንዳይመራ አድርጎታል። ግጭቱ ይህ ሪፖርት ይፋ በተደረገበት ወቅትም የቀጠለ እና እልባት ያልተበጀለት በመሆኑ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ቀውሱ መባባሱ በሪፖርቱ ተመላክቷል።

በኦሮሚያ ክልል በተደጋጋሚ በታጣቂዎች በሚፈጸሙ ጥቃቶች፤ የቤት እንስሳትና የንብረት ዝርፊያዎች፣ ቤቶችን የማቃጠልና ነዋሪዎችን በኃይል ማፈናቀል እና ቤተ-እምነቶችን ማቃጠል ምክንያት ኅብረተሰቡ በአካባቢው ተረጋግቶ የዕለት ተዕለት ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ሕይወቱን እንዳይመራ ማድረጉንና በርካታ ሰዎች ያለመጠለያ እንዲኖሩ፤ የሕክምና አገልግሎት እንዳያገኙ እና ሕፃናት ከትምህርት ገበታ ውጭ እንዲሆኑ ምክንያት እንደሆነ በሪፖርቱ ተብራርቷል።

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የጸጥታና ደኅንነት ሥጋት በሚል እና በሌሎች ምክንያቶች የንግድና የመኖሪያ ቤቶች በማፍረስ ሂደት ልዩ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው አካል ጉዳተኞች ሳይቀር የንግድ ቤቶቻቸው ያላግባብ እንዲፈርሱ መደረጉና ንብረታቸው መወሰዱ በገቢያቸውና በኑሯቸው ላይ ተጽዕኖ አሳድሯል።

በኦሮሚያ፣ በሶማሊ እና በተለያዩ የደቡብ እና ደቡብ ምዕራብ ክልሎች አካባቢዎች ባለፉት ሦስት ዓመታት ከፍተኛ ድርቅ በመከሰቱ የሕብረተሰቡ መተዳደሪያ የሆኑ በርካታ ቁጥር ያላቸው የቤት እንስሳት ሞተዋል፤ ነዋሪዎችም ከመኖሪያ ቀያቸው ተፈናቅለዋል። በመንግሥት በኩል ለችግሮቹ መፍትሔ ለማፈላለግ የተለያዩ ሙከራዎች ቢደረጉም የቅድመ መከላከል ሥራ በበቂ ሁኔታ ባለመተግበሩ ችግሩን የከፋ እንዲሆን እንዳደረገው በሪፖርቱ ተጠቁሟል። የኢሰመኮ የሲቪል፣ የፖለቲካ እና ማኅበራዊ-ኢኮኖሚያዊ መብቶች ኮሚሽነር ዶ/ር አብዲ ጅብሪል በ2015 ዓ.ም. በኮሚሽኑ የቀረቡ ምክረ ሐሳቦችን ከመተግበር ረገድ አበረታች ተግባራት መስተዋላቸውን ገልጸው የትምህርት፣ የጤና፣ ንብረት የማፍራት፣ በቂ በሆነ የኑሮ ደረጃ የመኖር፣ የሥራና ተያያዥ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ መብቶች እንዲከበሩ የፖሊሲና የሕግ ማሻሻያ ማድረግ እንዲሁም ጠንካራ የክትትልና የድጋፍ ሥርዓት መዘርጋት ያስፈልጋል ብለዋል።

የማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ መብቶች ሁኔታ ዓመታዊ ሪፖርት

Related posts

September 6, 2023September 6, 2023 Press Release
የአካል ጉዳተኞች እና አረጋውያን መብቶችን በተመለከተ አስቻይ የሕግ እና ተቋማዊ ማእቀፎች ሊቀረጹ ይገባል
February 21, 2023February 21, 2023 Press Release
ኢሰመኮ ለመጀመሪያ ጊዜ ያከናወነውን የአረጋውያን እንክብካቤ ማእከላት የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ክትትል ሪፖርት ይፋ አደረገ
July 12, 2023August 28, 2023 Press Release
ኢሰመኮ ቀዳሚው ትኩረት ለሰብአዊ መብቶች ጥሰት ዋነኛ ምክንያት የሆኑ የሥር መንስኤዎችን ለመፍታት ሊሆን እንደሚገባ አሳሰበ
December 25, 2020February 11, 2023 Press Release
ኮንሶ ዞን፡ በተደጋጋሚ የሚያገረሹ ግጭቶችና የሰብአዊ መብቶች ቀውስ

Signup for the Latest Update from EHRC

Submit your email to singup
Facebook Like us on FacebookXFollow us on XYouTube Follow us on YouTubeLinkedin Follow us on LinkedinWhatsApp WhatsAppTikTok TikTokTelegram TelegramInstagram InstagramFlicker Flickr

Useful Links

  • NANHRI
  • GANHRI
  • OHCHR
  • ACHPR
  • TRANSITIONAL JUSTICE

Get Involved

  • Jobs
  • Events
  • Contact Us
  • Telegram Bot
  • Subscribe to our newsletter

Connect with Us

  • Facebook
  • Twitter
  • LinkedIn
  • YouTube
  • Flickr
  • Instagram
Descriptive Text

We are an independent
national human rights
institution tasked with
the promotion and protection of human
rights in Ethiopia.

Submit your email to get the latest update from EHRC

Address: Sunshine Tower No. 5, Meskel Square, on Bole Road next to Hyatt Regency Hotel, Addis Ababa, Ethiopia
Tel: +251115504031 | Fax: +251 11 550 4125 | PO Box 1165 Addis Ababa | Email: info@ehrc.org


The contents of this website, excepting third party content for which the Commission bears no responsibility,
may be freely used and copied for educational and other non-commercial purposes, provided that any such reproduction is accompanied by an acknowledgement of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC). Source of images used in the content of this website: EHRC Media and Communications Department Archive and Creative Common License.

This website is managed by the Media and Communications team of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC).

We are using cookies to give you the best experience on our website.

You can find out more about which cookies we are using or switch them off in .

Scroll to top
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
    • Addis Ababa
    • Afar
    • Amhara
    • Benishangul Gumuz
    • Central Ethiopia
    • Dire Dawa
    • Gambella
    • Harari
    • Oromia
    • Sidama
    • Somali
    • South Ethiopia
    • South West Ethiopia Peoples’
    • Tigray
  • Areas of Work
    • Economic, Social & Cultural Rights
    • Civil & Political Rights
    • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
    • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
    • Human Rights Monitoring & Investigation
    • Women’s & Children’s Rights
    • Human Rights Education
    • Human Rights Film Festival
    • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Search
Ethiopian Human Rights Commission - EHRC
Powered by  GDPR Cookie Compliance
Privacy Overview

This website uses cookies so that we can provide you with the best user experience possible. Cookie information is stored in your browser and performs functions such as recognising you when you return to our website and helping our team to understand which sections of the website you find most interesting and useful.

Strictly Necessary Cookies

Strictly Necessary Cookie should be enabled at all times so that we can save your preferences for cookie settings.

If you disable this cookie, we will not be able to save your preferences. This means that every time you visit this website you will need to enable or disable cookies again.