Skip to content
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Ethiopian Human Rights Commission – EHRC
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
        • Regions

          EHRC is an independent federal institution tasked with the promotion and protection of human rights in Ethiopia.

        • Addis Ababa
        • Afar
        • Amhara
        • Benishangul Gumuz
        • Gambella
        • Oromia
        • Somali
        • Tigray
        • Central Ethiopia
        • Dire Dawa
        • Harari
        • Sidama
        • South Ethiopia
        • South West Ethiopia Peoples'
  • Areas of Work
        • Areas of Work

          We are an independent national human rights institution tasked with the promotion & protection of human rights in Ethiopia.

        • Economic, Social & Cultural Rights
        • Civil & Political Rights
        • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
        • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
        • Women’s & Children’s Rights
        • Human Rights Education
        • Human Rights Monitoring & Investigation
        • Human Rights Film Festival
        • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
 
Ethiopian Human Rights Commission – EHRCEthiopian Human Rights Commission – EHRC

ኢትዮጵያ በተ.መ.ድ. የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤት የምታቀርበው ረቂቅ ሪፖርት ላይ የተካሄደ ውይይት

July 13, 2024July 16, 2024 Event Update

ሁሉ-አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ወቅታዊ ግምገማ ረቂቅ ሪፖርት ዝግጅት ሂደት ግልጽ እና አሳታፊ እንዲሆን ያስፈልጋል

Twitter Facebook Telegram Email Whatsapp Print

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከፍትሕ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ኢትዮጵያ በ2017 ዓ.ም. በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤት (United Nations Human Rights Council – UNHRC) ላይ በምታቀርበው ሁሉ-አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ወቅታዊ ግምገማ (Universal Periodic Review- UPR) ረቂቅ ሪፖርት ላይ ከባለድርሻዎች ጋር ሐምሌ 4 ቀን 2016 ዓ.ም. ውይይት አካሂዷል። ረቂቅ ሪፖርቱ በፍትሕ ሚኒስቴር አስተባባሪነት የተዘጋጀ ሲሆን የተለያዩ የፌዴራል እና የክልል ዘርፍ መሥሪያ ቤቶች፣ የሲቪክ ማኅበራት እና የሌሎች ባለድርሻ አካላት ተወካዮች በተገኙበት ለውይይት ቀርቧል።  

የውይይቱ ተሳታፊዎች

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተ.መ.ድ.) ሁሉ-አቀፍ ወቅታዊ የግምገማ መድረክ (UPR) በተ.መ.ድ. የጠቅላላ ጉባኤ በመጋቢት ወር 1998 ዓ.ም. የተቋቋመ ሲሆን፣ ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ስምምነቶችን ተቀብለው እና አጽድቀው የሀገራቸው የሕግ አካል ያደረጉ አባል ሀገራት የገቡትን ቃል አተገባበር እና አፈጻጸም ደረጃ እርስ በራሳቸው የሚገማገሙበትና እና ተቀብለው ያላጸደቋቸውን ዓለም አቀፍ ስምምነቶች እንዲፈርሙ ምክረ ሐሳብ የሚለዋወበት መድረክ ነው። ሂደቱን በየ2 ዓመቱ በሚካሄድ ምርጫ የሚመረጡ 47 ሀገራት አባል የሆኑበት የተ.መ.ድ. የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤት (UNHRC) ያስተባብረዋል። 

ኢትዮጵያ በምክር ቤቱ 4ኛ ዙር ሁሉ-አቀፍ ወቅታዊ የግምገማ መድረክ ላይ የምታቀርበው ሪፖርት እ.ኤ.አ. በ2019 3ኛ ዙር ሪፖርት ባቀረበችበት ወቅት የተሰጧትን ምክረ ሐሳቦች አፈጻጸም ክትትል፣ እንዲሁም የሰብአዊ መብቶች ሁኔታን በማሻሻል ረገድ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተሠሩ ሥራዎችን በዝርዝር የሚያስረዳ መሆን ይጠበቅበታል። በዚሁ መሠረት የውይይት መድረኩ በረቂቅ ሪፖርቱ የሚካተቱ የቅርብ ጊዜ መረጃን ለመሰብሰብ፣ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ስምምነት መሠረት ግዴታዋን በትክክል እየተወጣች ስለመሆኑ ለመለየት፣ ያልተካተቱ የሰብአዊ መብቶች ጉዳዮች እንዲካተቱ እና የሚቀርበው ሪፖርት የበለጠ ሀገራዊ ሁኔታውን የሚገልጽ ለማድረግ ግብአት ለመሰብሰብ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።  

የፍትሕ ሚኒስቴር የመንግሥት ሕግና ፍትሕ አገልግሎት ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ አቶ በላይሁን ይርጋ

በውይይት መድረኩ የሁሉ-አቀፍ ወቅታዊ ግምገማ ረቂቅ ሪፖርት ማብራሪያ ቀርቦ፣ ኢትዮጵያ ተቀብላ ያጸደቀቻቸው እና ያላጸደቀቻቸው የሰብአዊ መብቶች ስምምነቶች፣ እንዲሁም ከዚህ ቀደም ለሁሉ-አቀፍ ወቅታዊ የግምገማ መድረክ ያቀረበቻቸው ሪፖርቶች እና የተሰጡ ምክረ ሐሳቦች ተዳስሰዋል። በ3ኛ ዙር በቀረበው ሪፖርት ላይ 327 ምክረ ሐሳቦች ለኢትዮጵያ የተሰጡ መሆናቸውን፤ ከእነዚህም መካከል 270 ምክረ ሐሳቦችን እንደተቀበለች እና 57ቱን ደግሞ ከግምት ውስጥ እንደምታስገባ ማሳዋቋ ተገልጿል። ማብራሪያውን ተከትሎ ተሳታፊዎች ከሚመለከታቸው የሰብአዊ መብቶች ዘርፍ አንጻር በ4 ቡድኖች ተከፍለው በረቂቅ ሪፖርቱ ላይ ውይይት በማድረግ አስተያየት እና ግብአት ሰጥተዋል።  

በፍትሕ ሚኒስቴር የመንግሥት ሕግ እና ፍትሕ አገልግሎት ዘርፍ ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ በላይሁን ይርጋ ሀገሪቱ የተለያዩ አህጉራዊ እና ዓለማ አቀፋዊ የሰብአዊ መብቶች ስምምነቶች ተቀብላ ማጽደቋን ጠቅሰው፣ እነዚህን ስምምነቶች መቀበል ደግሞ መብቶችን ማክበር፣ ማስከበር እና ማስፋፋት እንዲሁም ሪፖርት የማቅረብ ግዴታ የሚጥል በመሆኑ ኢትዮጵያ ለ4ኛ ጊዜ የምታቀርበው ሁሉ-አቀፍ ወቅታዊ ግምገማ ሪፖርት ይሄን ግዴታ የመወጣት አካል መሆኑን ጠቁመዋል።  

የኢሰመኮ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ

የኢሰመኮ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ በበኩላቸው ሁሉ-አቀፍ ወቅታዊ ግምገማ የሰብአዊ መብቶች አያያዝ እና አጠባበቅ ክፍተት ለመለየት እንዲሁም ከሌሎች ሀገራት የሰብአዊ መብቶች አያያዝ ልምድ ለመቅሰም ያለውን ጠቀሜታ ጠቁመው፣ ለ4ኛ ዙር በሚቀርበው ሪፖርት መካተት የሚገባቸው ነጥቦች በአግባቡ እንዲነሱ ኢሰመኮ እንደ ብሔራዊ ሰብአዊ መብቶች ተቋም እንዲህ ያሉ አስቻይ መድረኮችን መፍጠር እና እገዛ የማድረግ ኃላፊነት ያለበት መሆኑን ገልጸዋል። አክለውም ሁሉ-አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ወቅታዊ ግምገማ ሪፖርት ዝግጅት ሂደት ግልጽ እና አሳታፊ እንዲሆን ያስፈልጋል ብለዋል። 

Related posts

June 5, 2022October 6, 2022 Press Release
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተ.መ.ድ.) ሁሉን-አቀፍ የግምገማ መድረክ (Universal Periodic Review) ላይ የሲቪል ማኅበራት ሚና ማጎልበት
October 23, 2023October 27, 2023 Event Update
በብሔራዊ የንግድ እና ሰብአዊ መብቶች የድርጊት መርኃ ግብር ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር የተካሄደ ውይይት
May 19, 2023August 28, 2023 Event Update
ኢሰመኮ የግል የጤና ተቋማት የፋይናንስ ተደራሽነት እና የጤና መብት አተገባበር ሁኔታን በተመለከተ ባከናወነው ክትትል ሪፖርት ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሄደ
September 6, 2022October 7, 2022 Event Update
የአፍሪካ የሰዎች እና ሕዝቦች መብቶች ቻርተር እና የአፍሪካ የሴቶች መብቶች ፕሮቶኮል አፈጻጸምን አስመልክቶ በአባል ሀገር መንግሥታት ለአፍሪካ የሰዎች እና የሕዝቦች መብቶች ኮሚሽን በሚቀርበው ወቅታዊ ዘገባ አዘገጃጀት ዙሪያ የተዘጋጀ አውደ ጥናት

Signup for the Latest Update from EHRC

Submit your email to singup
Facebook Like us on FacebookXFollow us on XYouTube Follow us on YouTubeLinkedin Follow us on LinkedinWhatsApp WhatsAppTikTok TikTokTelegram TelegramInstagram InstagramFlicker Flickr

Useful Links

  • NANHRI
  • GANHRI
  • OHCHR
  • ACHPR
  • TRANSITIONAL JUSTICE

Get Involved

  • Jobs
  • Events
  • Contact Us
  • Telegram Bot
  • Subscribe to our newsletter

Connect with Us

  • Facebook
  • Twitter
  • LinkedIn
  • YouTube
  • Flickr
  • Instagram
Descriptive Text

We are an independent
national human rights
institution tasked with
the promotion and protection of human
rights in Ethiopia.

Submit your email to get the latest update from EHRC

Address: Sunshine Tower No. 5, Meskel Square, on Bole Road next to Hyatt Regency Hotel, Addis Ababa, Ethiopia
Tel: +251115504031 | Fax: +251 11 550 4125 | PO Box 1165 Addis Ababa | Email: info@ehrc.org


The contents of this website, excepting third party content for which the Commission bears no responsibility,
may be freely used and copied for educational and other non-commercial purposes, provided that any such reproduction is accompanied by an acknowledgement of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC). Source of images used in the content of this website: EHRC Media and Communications Department Archive and Creative Common License.

This website is managed by the Media and Communications team of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC).

We are using cookies to give you the best experience on our website.

You can find out more about which cookies we are using or switch them off in .

Scroll to top
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
    • Addis Ababa
    • Afar
    • Amhara
    • Benishangul Gumuz
    • Central Ethiopia
    • Dire Dawa
    • Gambella
    • Harari
    • Oromia
    • Sidama
    • Somali
    • South Ethiopia
    • South West Ethiopia Peoples’
    • Tigray
  • Areas of Work
    • Economic, Social & Cultural Rights
    • Civil & Political Rights
    • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
    • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
    • Human Rights Monitoring & Investigation
    • Women’s & Children’s Rights
    • Human Rights Education
    • Human Rights Film Festival
    • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Search
Ethiopian Human Rights Commission - EHRC
Powered by  GDPR Cookie Compliance
Privacy Overview

This website uses cookies so that we can provide you with the best user experience possible. Cookie information is stored in your browser and performs functions such as recognising you when you return to our website and helping our team to understand which sections of the website you find most interesting and useful.

Strictly Necessary Cookies

Strictly Necessary Cookie should be enabled at all times so that we can save your preferences for cookie settings.

If you disable this cookie, we will not be able to save your preferences. This means that every time you visit this website you will need to enable or disable cookies again.