Skip to content
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Ethiopian Human Rights Commission – EHRC
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
        • Regions

          EHRC is an independent federal institution tasked with the promotion and protection of human rights in Ethiopia.

        • Addis Ababa
        • Afar
        • Amhara
        • Benishangul Gumuz
        • Gambella
        • Oromia
        • Somali
        • Tigray
        • Central Ethiopia
        • Dire Dawa
        • Harari
        • Sidama
        • South Ethiopia
        • South West Ethiopia Peoples'
  • Areas of Work
        • Areas of Work

          We are an independent national human rights institution tasked with the promotion & protection of human rights in Ethiopia.

        • Economic, Social & Cultural Rights
        • Civil & Political Rights
        • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
        • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
        • Women’s & Children’s Rights
        • Human Rights Education
        • Human Rights Monitoring & Investigation
        • Human Rights Film Festival
        • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
 
Ethiopian Human Rights Commission – EHRCEthiopian Human Rights Commission – EHRC

የማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ መብቶች ሁኔታ ዓመታዊ ሪፖርት

October 30, 2024October 30, 2024 Press Release, Report

ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ጉዳዮችን የሚመለከቱ ውሳኔዎችና እርምጃዎች ሕጋዊ አካሄድን የተከተሉ እና ከባለመብቶች ጋር ተገቢው ውይይት የተደረገባቸው ሊሆኑ ይገባል

Twitter Facebook Telegram Email Whatsapp Download Print

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ሰኔ 28 ቀን 2016 ዓ.ም. ይፋ ካደረገው 3ኛው የኢትዮጵያ ዓመታዊ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ሪፖርት በተጨማሪ የማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መብቶች ሁኔታ ላይ የሚያተኩር ባለ 26 ገጽ ዓመታዊ የዘርፍ ሪፖርት ዛሬ ይፋ አድርጓል። ሪፖርቱ ከሰኔ ወር 2015 ዓ.ም. እስከ ሰኔ ወር 2016 ዓ.ም. ያለውን ጊዜ የሚሸፍን ሲሆን፣ ኢሰመኮ በሕግ በተሰጠው ሥልጣን፣ ተግባርና ኃላፊነት መሠረት በበጀት ዓመቱ የተቀበላቸውን አቤቱታዎች፣ ያከናወናቸውን የተለያዩ የሰብአዊ መብቶች ክትትሎች፣ ምርመራዎች፣ ጥናቶች፣ የውትወታ ሥራዎች፣ በምክክር መድረኮች የተገኙ ግብአቶች እና አግባብነት ያላቸው ሰነዶችና ሌሎች የመረጃ ምንጮችን መሠረት በማድረግ የተዘጋጀ ነው። 

በ2016 በጀት ዓመት ከማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መብቶች መከበር፣ መጠበቅና መስፋፋት አኳያ መልካም እመርታዎች መኖራቸው በሪፖርቱ ተገልጿል። መንግሥት የንግድ እና ሰብአዊ መብቶች የድርጊት መርኃ-ግብር ዝግጅት መጀመሩ፤ የዓለም አቀፍ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና የባህል መብቶች ቃልኪዳን አፈጻጸምን በተመለከተ ለዓለም አቀፉ የኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና የባህል መብቶች ኮሚቴ ሊቀርብ የሚገባውን ሪፖርት ለማቅረብ ዝግጀት መጀመሩ፤ የጤና ፖሊሲው ሰብአዊ መብቶች ተኮር በሆነ መልኩ መቀረጹ፤ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅ የባለይዞታዎችን መብቶች የሚያስፋፉ ድንጋጌዎችን ባካተተ መልኩ መጽደቁ፤ እንዲሁም የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ የተከራዮችን ዐቅም ባገናዘበና የመኖሪያ ቤት መብትን ለማረጋገጥ በሚያግዝ ሁኔታ ሥራ ላይ መዋሉ በሪፖርቱ ከተካተቱ ቁልፍ እመርታዎች መካከል ይገኙበታል። በተጨማሪም፣ ከግጭት እና ከመምህራን ደመወዝ አለመከፈል ጋር ተያይዞ ትምህርት በተቋረጠባቸው አካባቢዎች ትምህርት እንዲጀመር ለማድረግ በመንግሥት በኩል ጥረቶች መደረጋቸው በሪፖርቱ ተጠቁሟል። 

በሌላ በኩል ሪፖርቱ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መብቶችን በማረጋገጥ ረገድ ያሉ አሳሳቢ ሁኔታዎችን ለይቷል። ከነሐሴ ወር 2015 ዓ.ም. ጀምሮ በአማራ ክልል ከተከሰተው የትጥቅ ግጭት እና በሌሎች ክልሎችም ከቀጠለው የጸጥታ ችግር ጋር በተያያዘ መኖሪያ ቤትና የመተዳደሪያ ንብረቶችን ጨምሮ በመሠረተ ልማቶችና የአገልግሎት ተቋማት ላይ ውድመት የደረሰ ሲሆን በተለይም በምግብ፣ በጤና፣ በንብረት፣ በትምህርት፣ በሥራና ተያያዥ መብቶች ላይ ጉዳት አድርሷል። አፋር፣ አማራ እና ትግራይ ክልሎችን ጨምሮ በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች የተከሰተው ድርቅ ከግጭትና ከጸጥታ ችግር ጋር በተያያዘ ከሚከሰት የምርት መቀዛቀዝ እንዲሁም የመሠረታዊ ሸቀጦች ዋጋ ንረት ጋር ተዳምሮ በርካታ ሰዎችን ለምግብ እጥረት ዳርጓል። ከባድ ዝናብ ያስከተለው ጎርፍ ለምሳሌ በደቡብ እና ምሥራቅ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በሚኖሩ ሰዎች ላይ በተለይም በሶማሊ ክልል የሰው ሕይወት ኅልፈት እና በመሠረታዊ አገልግሎቶች ላይ ጉዳት አስከትሏል። በሀገሪቱ የተወሰኑ ክፍሎች የተከሰተው የወባ፣ ኮሌራና ኩፍኝ ወረርሽኝ የጤና መብት ሁኔታን አሳሳቢ ማድረጉ፣ በ2016 በጀት ዓመት ለማኅበራዊ አገልግሎቶች የተመደበው በጀት ከ2015 በጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር በመቶኛ ያለው ድርሻ መቀነሱ፣ በተለያዩ አካባቢዎች በተከሰቱ ግጭቶች እና የተፈጥሮ አደጋዎች ምክንያት ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ትምህርት ቤቶች መዘጋታቸውና በርካታ ሕፃናት ከትምህርት ውጪ መሆናቸው፣ አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ ከተሞች በርካታ የንግድና መኖሪያ ቤቶች ሕጋዊ ሂደትን ባልተከተለ መልኩ እንዲፈርሱ መደረጋቸው እና የሠራተኞች ደመወዝ በወቅቱና በአግባቡ ባለመከፈሉ ምክንያት ሠራተኞች ለተለያዩ ችግሮች መዳረጋቸው በሪፖርቱ ከተመላከቱ ዋና ዋና ተግዳሮቶች እና አሳሳቢ ጉዳዮች መካከል ናቸው።  

በሪፖርቱ መንግሥት በበጀት ዓመቱ የታዩ አሳሳቢ ሁኔታዎችን በመቅረፍ የማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መብቶችን በተሟላ ሁኔታ እውን እንዲያደርግ እና ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ጉዳዮችን የሚመለከቱ ውሳኔዎችና እርምጃዎች ሕጋዊ ሁኔታን በተከተለ መልኩ ከባለመብቶች ጋር ተገቢው ውይይት ተደርጎ እንዲወሰዱ የሚሉ እና ሌሎች ምክረ ሐሳቦች ቀርበዋል። የሲቪል፣ የፖለቲካ፣ የማኅበራዊ-ኢኮኖሚያዊ መብቶች ኮሚሽነር ዶ/ር አብዲ ጅብሪል ኢሰመኮ በክትትልና በምርመራና ሥራዎቹ ላይ ተመሥርቶ የሚያቀርባቸውን ምክረ ሐሳቦች በከፍተኛ ትኩረት፣ ዕቅድና ቅንጅት መተግበር አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰው፣ በተለይም በሰው ሠራሽ እና በተፈጥሮ አደጋዎች ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸው ተቋማት መልሰው እንዲቋቋሙና የተሟላ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ መንግሥት አስፈላጊ እርምጃዎችን ሁሉ እንዲወስድ ጥሪ አቅርበዋል።  

የማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ መብቶች ሁኔታ ዓመታዊ ሪፖርት (ከሰኔ ወር 2015 ዓ.ም. እስከ ሰኔ ወር 2016 ዓ.ም.)

Related posts

September 15, 2023September 15, 2023 Press Release
ኢሰመኮ ለመጀመሪያ ጊዜ ያዘጋጀውን የማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መብቶች ሁኔታ ዓመታዊ ሪፖርት ይፋ አደረገ
October 25, 2024October 28, 2024 Press Release
የሴቶች እና የሕፃናት ሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ዓመታዊ ሪፖርት
September 6, 2023September 6, 2023 Press Release
የአካል ጉዳተኞች እና አረጋውያን መብቶችን በተመለከተ አስቻይ የሕግ እና ተቋማዊ ማእቀፎች ሊቀረጹ ይገባል
July 5, 2024November 19, 2024 Press Release
የትጥቅ ግጭቶች ለሰብአዊ መብቶች ጥሰት ዋነኛ ምክንያት ሆነው በመቀጠላቸው ግልጽ፣ አካታች እና ተዓማኒ የሆነ ሰላማዊ መፍትሔ እና የሽግግር ፍትሕ ሂደት አፋጣኝ አስፈላጊነት አመላካች ነው

Signup for the Latest Update from EHRC

Submit your email to singup
Facebook Like us on FacebookXFollow us on XYouTube Follow us on YouTubeLinkedin Follow us on LinkedinWhatsApp WhatsAppTikTok TikTokTelegram TelegramInstagram InstagramFlicker Flickr

Useful Links

  • NANHRI
  • GANHRI
  • OHCHR
  • ACHPR
  • TRANSITIONAL JUSTICE

Get Involved

  • Jobs
  • Events
  • Contact Us
  • Telegram Bot
  • Subscribe to our newsletter

Connect with Us

  • Facebook
  • Twitter
  • LinkedIn
  • YouTube
  • Flickr
  • Instagram
Descriptive Text

We are an independent
national human rights
institution tasked with
the promotion and protection of human
rights in Ethiopia.

Submit your email to get the latest update from EHRC

Address: Sunshine Tower No. 5, Meskel Square, on Bole Road next to Hyatt Regency Hotel, Addis Ababa, Ethiopia
Tel: +251115504031 | Fax: +251 11 550 4125 | PO Box 1165 Addis Ababa | Email: info@ehrc.org


The contents of this website, excepting third party content for which the Commission bears no responsibility,
may be freely used and copied for educational and other non-commercial purposes, provided that any such reproduction is accompanied by an acknowledgement of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC). Source of images used in the content of this website: EHRC Media and Communications Department Archive and Creative Common License.

This website is managed by the Media and Communications team of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC).

We are using cookies to give you the best experience on our website.

You can find out more about which cookies we are using or switch them off in .

Scroll to top
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
    • Addis Ababa
    • Afar
    • Amhara
    • Benishangul Gumuz
    • Central Ethiopia
    • Dire Dawa
    • Gambella
    • Harari
    • Oromia
    • Sidama
    • Somali
    • South Ethiopia
    • South West Ethiopia Peoples’
    • Tigray
  • Areas of Work
    • Economic, Social & Cultural Rights
    • Civil & Political Rights
    • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
    • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
    • Human Rights Monitoring & Investigation
    • Women’s & Children’s Rights
    • Human Rights Education
    • Human Rights Film Festival
    • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Search
Ethiopian Human Rights Commission - EHRC
Powered by  GDPR Cookie Compliance
Privacy Overview

This website uses cookies so that we can provide you with the best user experience possible. Cookie information is stored in your browser and performs functions such as recognising you when you return to our website and helping our team to understand which sections of the website you find most interesting and useful.

Strictly Necessary Cookies

Strictly Necessary Cookie should be enabled at all times so that we can save your preferences for cookie settings.

If you disable this cookie, we will not be able to save your preferences. This means that every time you visit this website you will need to enable or disable cookies again.