Skip to content
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Ethiopian Human Rights Commission – EHRC
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
        • Regions

          EHRC is an independent federal institution tasked with the promotion and protection of human rights in Ethiopia.

        • Addis Ababa
        • Afar
        • Amhara
        • Benishangul Gumuz
        • Gambella
        • Oromia
        • Somali
        • Tigray
        • Central Ethiopia
        • Dire Dawa
        • Harari
        • Sidama
        • South Ethiopia
        • South West Ethiopia Peoples'
  • Areas of Work
        • Areas of Work

          We are an independent national human rights institution tasked with the promotion & protection of human rights in Ethiopia.

        • Economic, Social & Cultural Rights
        • Civil & Political Rights
        • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
        • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
        • Women’s & Children’s Rights
        • Human Rights Education
        • Human Rights Monitoring & Investigation
        • Human Rights Film Festival
        • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
 
Ethiopian Human Rights Commission – EHRCEthiopian Human Rights Commission – EHRC

የሰላም ግንባታና የሽግግር ፍትሕ ሂደት በግጭቶች ውስጥ ለተፈጸሙ ጾታዊ ጥቃቶች ተጠያቂነትን እና የተጎጂዎችን ውጤታማ መፍትሔ የማግኘት መብትን በአግባቡ ማረጋገጥ ይጠበቅበታል

December 6, 2022December 6, 2022 Public Statement

በየዓመቱ ከኅዳር 16 – ታኅሣሥ 1 የሚታሰበው የ16ቱ ቀናት የፀረ ጾታዊ ጥቃት ዘመቻ በዓለም አቀፍ ደረጃ በመካሄድ ላይ ሲሆን በኢትዮጵያም በብዙ ባለድርሻ አካላት በልዩ ልዩ እንቅስቃሴዎች እየተካሄደ ነው

Twitter Facebook Telegram Email Whatsapp Print

በተለይም ሀገራችን አሁን በምትገኝበት የሰሜኑ ኢትዮጵያ የሰላም ስምምነትና ድኅረ -ግጭት ዓውድ፤ የሰላም ግንባታ እንዲሁም የሽግግር ፍትሕ ማዕቀፎች በጦርነት ዓውድ ውስጥ ለተፈጸሙ ጾታዊ ጥቃቶች ተጠያቂነትን፣ እንዲሁም የተጎጂዎችን የተሟላ ፍትሕ እና ውጤታማ መፍትሔ የማግኘት መብትን (right to effective remedy) ባረጋገጠ መልኩ እንዲተገበር እጅግ አስፈላጊ በመሆኑ፤ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በዚሁ አጋጣሚ ከዚህ በፊት ስለ ሽግግር ወቅት የፍትሕ አስተዳደር ያቀረባቸውን ምክረ ሃሳቦችና በተለይም ስለ ጾታዊ ጥቃቶች ተጠያቂነት ሊሰጥ የሚገባውን ልዩ ትኩረት በድጋሚ ለማስታወስ ይወዳል።

የሰላም ግንባታ እና የሽግግር ፍትሕ ሂደቶች ግጭቶች በዘላቂነት የሚፈቱበትን መንገድ እና ለተፈጸሙ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች የተጠያቂነት ማዕቀፍ የሚዘረጋበትን ሥርዓት በመቀየስ ረገድ ወሳኝ ሚና ይጫወታሉ። ይህም በግጭቶች ዓውድ የሚፈጸሙ ጾታዊ ጥቃቶችን ለመከላከል፣ የተፈጸሙ ጥቃቶችን ባሕርይ፣ ክብደት እና የጉዳት መጠንን መሠረት ያደረገ የተጠያቂነት ማዕቀፍ ለመዘርጋት፤ ተጎጂዎችን ማዕከል ያደረገ ውጤታማ መፍትሔ እና የድኅረ-ግጭት መልሶ ማቋቋም ሥርዓት ለመንደፍ የሚያስችል መደላድል ይፈጥራል። 

በኢትዮጵያ በተከሰቱ ግጭቶች በተለይም አስከፊ ጦርነት በተካሄደባቸው በትግራይ፣ አፋር እና አማራ ክልሎች ወሲባዊ ጥቃቶች እና በሴቶች ላይ ያነጣጠሩ ግፍና ጭካኔ የተሞላባቸው የጾታዊ ጥቃት ተግባራት የስልታዊነት አዝማሚያ እንዳሳዩ የኮሚሽኑ ግኝቶች ጠቁመዋል። በርካታ ሴቶች ላይ ለተፈጸሙት መጠነ-ሰፊ እና ስልታዊ ጥቃቶች ምላሽ ከመስጠት አኳያ ተጎጂዎችን ማዕከል ያደረገ የተሟላ የፍትሕ እና የዘላቂ ተሀድሶ ሂደት መሠረታዊ ነው። 

የሰሜን ኢትዮጵያው ግጭት የሰላም ስምምነት በአንቀጽ 10 (3) እንደሚገልጸው የኢትዮጵያ መንግሥት የተጠያቂነት፣ የእውነትን ማረጋገጥ፣ የተጎጂዎችን ማካካሻ፣ ዕርቅ እና መፈወስ ያለመ አጠቃላይ ሀገራዊ የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ ተግባራዊ ለማድረግ አልሟል። ከሽግግር ፍትሕ ዋና ዋና ስልቶች መካከልም አንዱ ተጠያቂነት እንደመሆኑ መጠን ስምምነቱ ተጠያቂነትን በግልጽ ታሳቢ ያደረገ የሽግግር ፍትሕ ሂደትን ለመቀየስ ያለመ መሆኑ በጦርነቱ ውስጥ በተከሰቱ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች ተጎጂ ለሆኑት ሴቶች ተስፋን የሚሰጥ ነው፡፡ ይህን ተስፋ ዕውን ለማድረግ በግጭት ውስጥ ለተፈጸሙ ጾታዊ ጥቃቶች የተጠያቂነት ማዕቀፍን እና በቁልፍ ሂደቶች ውስጥ የተጎጂ ሴቶች ተሳትፎን በተመከለተ ግልጽ ፍኖት በአፋጣኝ ማስቀመጥ ያስፈልጋል። ይህ በሌለበት ሁኔታ የሚከናወኑ የሰላም ግንባታ እና የሽግግር ፍትሕ ጥረቶች ጾታን መሠረት ያደረጉ መድሎዎች እና ጥቃቶች እንዲቀጥሉ ያደርጋሉ። በተለይም በግጭት ወቅት የተፈጸሙ ጾታዊ ጥቃቶችን እና የወንጀል ድርጊቶችን ለመከላከል፣ የተፈጸሙትን ጥቃቶች እና የወንጀል ድርጊቶች ለመመርመር እና አጥፊዎችን ለመቅጣት፣ እንዲሁም ተጎጂዎችን መልሶ ለማቋቋም በመንግሥት በኩል የተሟሉ እርምጃዎች ገና የሚቀሩ ስለሆነ፤ በሴቶች ላይ አሁንም ሊደርሱ ለሚችሉ ጾታዊ ጥቃቶችና የተጋላጭነት ሁኔታዎች ልዩ ትኩረት መስጠት ያስፈልጋል። 

ስለሆነም በግጭት ወቅት ለተፈጸሙ ጾታዊ ጥቃቶች ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ፣ ተጎጂዎችን መልሶ ለማቋቋምና ለወደፊቱም መሰል ጾታዊ ጥቃቶችን ለመከላከል የሚከተሉትን ቁልፍ ነጥቦች ተግባራዊ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡

  1. ከሰብአዊ መብቶች ስምምነቶች ጋር በሚጣጣም መልኩ የሕግ እና የፍትሕ ሥርዓት ማሻሻያ ማድረግ

በግጭት ወቅት ለሚፈጸሙ ጾታዊ ጥቃቶች የሕግ ተጠያቂነትን በሚመለከት በሀገሪቱ የሕግ ማዕቀፍ ያሉትን ሰፊ ክፍተቶች ለመቅረፍ በአህጉራዊና ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ድንጋጌዎች መሠረት የሕግ ማሻሻያ ማድረግ ያስፈልጋል። እንዲሁም ለጾታዊ ጥቃቶች ምላሽ ከመስጠት አኳያ የፍትሕ ሥርዓቱን የውጤታማነት ችግሮችን ለመፍታት መንግሥት አስፈላጊውን የፍትሕ ሥርዓት ማሻሻያ በማድረግ በግጭት ወቅት በሴቶች እና ሕፃናት ላይ የተፈጸሙ ወሲባዊ እና ጾታዊ ጥቃቶችን ለመዳኘት የሰብአዊ መብቶች መርሆችን እና ዓለም አቀፍ ልምዶችን መሠረት ያደረገ የፍትሕ ሂደትን ተግባራዊ ማድረግ ይኖርበታል።

2. የተጎጂዎችን መብት ማዕከል ያደረገ የወንጀል ምርመራ ስልት ተግባራዊ ማድረግ

የጾታዊ ጥቃት ወንጀል ምርመራዎችን በአህጉራዊና ዓለም አቀፍ መመዘኛዎች መሠረት ለማከናወን አፋጣኝ፣ ገለልተኛ፣ ነጻ፣ የጾታዊ ጥቃቶች አፈጻጸም ውስብስብነትን ታሳቢ ያደረገ ውጤታማ የምርመራ ስልት ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል ሥርዓት መተግበር አስፈላጊ ነው፡፡ በመሆኑም መንግሥት በዓለም አቀፍ መመዘኛዎች መሠረት የተጎጂዎችን መብቶች ማዕከል ያደረገ፣ እንዲሁም የሥርዓተ-ጾታ ትንታኔዎችን እና የሴቶች መብቶች መስፈርቶችን ባካተተ መልኩ የምርመራ ሂደቱን በተገቢው ጥራት እና ወቅታዊነት ማከናወን ይኖርበታል።

3. ክስ መመስረትና አጥፊዎች ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኙ ማድረግ

መንግሥት በማናቸውም ጊዜ እና በተለይም በግጭት ወቅት የተፈጸሙ ጾታዊ ጥቃቶችን የመመርመር፣ ክስ የመመስረት እና የድርጊቱን ፈጻሚዎችን የመቅጣት ኃላፊነት አለበት። ስለዚህም ጾታዊ ጥቃት ለደረሰባቸው ሴቶች ፍትሕን ተደራሽ ለማድረግ አስፈላጊ የምርመራ እና ክስ የመመስረት ሥራዎች ወቅታዊ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡

4. ተጎጂዎችን ማዕከል ያደረገ የካሳና የተሐድሶ ማዕቀፍን ማረጋገጥ

መንግሥት ተገቢውን የሕግ ማዕቀፍ በመቅረጽ በግጭት ዓውድ ለተከሰቱ ጾታዊ ጥቃቶች ውጤታማ መፍትሔ ለመስጠት የሚያስችል የፍትሐ ብሔር አማራጭ፣ የትግበራ ማዕቀፍ፣ እንዲሁም ተጎጂዎች የማገገሚያ ወይም የተሐድሶ ድጎማ የሚያገኙበትን ሥርዓት መዘርጋት ይኖርበታል። 

5. ሕብረተሰቡን ማስተማር

ወሲባዊ ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶች የመድልዎ እና የዳግም ጥቃት ሰለባ በመሆናቸው መንግሥት ይህን ለመከላከል ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ሕብረተሰቡን ማስተማር፣ እንዲሁም መድልዎ እና መገለል የሚፈጽሙ ግለሰቦች እና ቡድኖችን ተጠያቂነት ማረጋገጥ ይጠበቅበታል።

6. የተቀናጀ የድጋፍ እርምጃዎችን መውሰድ

ከግጭቶች ጋር በተያያዘ የተጎዱ ሴቶችን እና ሕፃናትን ለመደገፍ፣ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ እና መልሶ ለማቋቋም የሚያስፈልጉ ሥራዎችን ለማስቀጠልና ለማስተባበር በተቋማት መካከል ያለው ቅንጅታዊ አሠራር የተጠናከረ፣ ውጤታማና ወቅታዊ ምላሽ ለመስጠት የሚስችል መሆን ይኖርበታል፡፡ በመሆኑም በግጭት ዐውድ ጥቃት ለደረሰባቸው ሴቶችና ሕፃናት የማገገሚያና መልሶ የማቋቋሚያ፣ የጤና እና የሥነ-ልቦና ድጋፍ፣ የፍትሕ እና ሌሎች አገልግሎቶች አቅርቦትን የማስተባበር ሥራ በፌዴራልና በክልል መንግሥታት መቀላጠፍ ይኖርበታል።’

7. ተአማኒ የሆነ የሽግግር ፍትሕ ሥርዓት መቀየስ እና ተግባራዊ ማድረግ

በግጭት ዓውድ ለተፈጸሙ መጠነ-ሰፊ እና ውስብስብ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች የተሟላ ፍትሕ እና ውጤታማ መፍትሔ ለመስጠት ግጭቶች እና ጥቃቶች እንዳያገረሹ በዘላቂነት ለመፍታት የሽግግር ፍትሕ ማዕቀፍ መዘርጋት አስፈላጊ ነው። ተጠያቂነት፣ የጉዳት ማካካሻ፣ ዕውነትን የማውጣትና የማወቅ እንዲሁም ሁለንተናዊ ማገገምን ማዕከል ያደረገ፣ በሰብአዊ መብቶች መርሆች እና በአህጉራዊና ዓለም አቀፍ የሽግግር ፍትሕ ማዕቀፎች ላይ የተመሠረተ ተአማኒነት ያለው ሀገር አቀፍ የሽግግር ፍትሕ ሥርዓት መቀየስ እና ተግባራዊ ማድረግ ይጠበቅበታል።

8. በሰላም ግንባታና በሽግግር ፍትሕ ወቅት ሴቶች ትርጉም ያለው ተሳትፎ እንዲኖራቸው እና ድምፃቸው እንዲካተት ማድረግ

የሴቶች ተሳትፎ ዘላቂ ሰላምን እና የተሟላ ፍትሕን ለማስፈን ወሳኝ ነወ። በሰላም ድርድርና ስምምነት እንዲሁም በሽግግር ፍትሕ ውስጥ በሁሉም ደረጃ እና የውሳኔ አሰጣጥ ሂደቶች የሴቶችን ትርጉም ያለው ተሳትፎ እና የውሳኔ ሰጪነት ሚና ማረጋገጥ ይገባል። ማናቸውም የሰላም እና የፍትሕ ማዕቀፍ ግንባታ ጥረቶች የተጎጂ ሴቶችን ጥያቄ፣ ፍላጎት እና ድምፅ በአግባቡ ያካተቱ መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡ አጠቃላይ የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን ሙሉ በሙሉ በመፍታት ጾታዊ እኩልነትን ማስፈን፣ በጾታዊ ጥቃቶች እና በሥርዓተ-ጾታ ላይ የተመሠረቱ ጥሰቶች እና ዋና መንስኤዎቻቸው ላይ ልዩ ትኩረት መስጠትም ያስፈልጋል።

Related posts

October 18, 2023October 23, 2023 Event Update
በምግብ ሥርዓት፣ ምግብ የማግኘት መብት እና ሰብአዊ መብትን መሠረት ያደረገ አቀራረብ ዙሪያ የተካሄዱ ስልጠናዎች
January 18, 2023August 28, 2023 Human Rights Concept
የሽግግር ፍትሕ
October 26, 2022October 26, 2022 Human Rights Concept
የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች እና ስደተኞች የሰብአዊ መብቶች ጥበቃ
March 17, 2022August 28, 2023 EHRC Quote
በግጭት/ጦርነት ወቅት የሚደርሱ ፆታዊ ጥቃቶች

Signup for the Latest Update from EHRC

Submit your email to singup
Facebook Like us on FacebookXFollow us on XYouTube Follow us on YouTubeLinkedin Follow us on LinkedinWhatsApp WhatsAppTikTok TikTokTelegram TelegramInstagram InstagramFlicker Flickr

Useful Links

  • NANHRI
  • GANHRI
  • OHCHR
  • ACHPR
  • TRANSITIONAL JUSTICE

Get Involved

  • Jobs
  • Events
  • Contact Us
  • Telegram Bot
  • Subscribe to our newsletter

Connect with Us

  • Facebook
  • Twitter
  • LinkedIn
  • YouTube
  • Flickr
  • Instagram
Descriptive Text

We are an independent
national human rights
institution tasked with
the promotion and protection of human
rights in Ethiopia.

Submit your email to get the latest update from EHRC

Address: Sunshine Tower No. 5, Meskel Square, on Bole Road next to Hyatt Regency Hotel, Addis Ababa, Ethiopia
Tel: +251115504031 | Fax: +251 11 550 4125 | PO Box 1165 Addis Ababa | Email: info@ehrc.org


The contents of this website, excepting third party content for which the Commission bears no responsibility,
may be freely used and copied for educational and other non-commercial purposes, provided that any such reproduction is accompanied by an acknowledgement of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC). Source of images used in the content of this website: EHRC Media and Communications Department Archive and Creative Common License.

This website is managed by the Media and Communications team of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC).

We are using cookies to give you the best experience on our website.

You can find out more about which cookies we are using or switch them off in .

Scroll to top
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
    • Addis Ababa
    • Afar
    • Amhara
    • Benishangul Gumuz
    • Central Ethiopia
    • Dire Dawa
    • Gambella
    • Harari
    • Oromia
    • Sidama
    • Somali
    • South Ethiopia
    • South West Ethiopia Peoples’
    • Tigray
  • Areas of Work
    • Economic, Social & Cultural Rights
    • Civil & Political Rights
    • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
    • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
    • Human Rights Monitoring & Investigation
    • Women’s & Children’s Rights
    • Human Rights Education
    • Human Rights Film Festival
    • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Search
Ethiopian Human Rights Commission - EHRC
Powered by  GDPR Cookie Compliance
Privacy Overview

This website uses cookies so that we can provide you with the best user experience possible. Cookie information is stored in your browser and performs functions such as recognising you when you return to our website and helping our team to understand which sections of the website you find most interesting and useful.

Strictly Necessary Cookies

Strictly Necessary Cookie should be enabled at all times so that we can save your preferences for cookie settings.

If you disable this cookie, we will not be able to save your preferences. This means that every time you visit this website you will need to enable or disable cookies again.