Skip to content
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Ethiopian Human Rights Commission – EHRC
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
        • Regions

          EHRC is an independent federal institution tasked with the promotion and protection of human rights in Ethiopia.

        • Addis Ababa
        • Afar
        • Amhara
        • Benishangul Gumuz
        • Gambella
        • Oromia
        • Somali
        • Tigray
        • Central Ethiopia
        • Dire Dawa
        • Harari
        • Sidama
        • South Ethiopia
        • South West Ethiopia Peoples'
  • Areas of Work
        • Areas of Work

          We are an independent national human rights institution tasked with the promotion & protection of human rights in Ethiopia.

        • Economic, Social & Cultural Rights
        • Civil & Political Rights
        • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
        • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
        • Women’s & Children’s Rights
        • Human Rights Education
        • Human Rights Monitoring & Investigation
        • Human Rights Film Festival
        • Human Rights Moot Court Competition
        • EHRC–CSO Coordination Platform
        • Transitional Justice
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
 
Ethiopian Human Rights Commission – EHRCEthiopian Human Rights Commission – EHRC

የኢሰመኮ የ2017 በጀት ዓመት የዘርፍ ሪፖርቶች

March 16, 2026March 16, 2026 Press Release, Report

የፖሊሲ፣ የሕግና የአሠራር ማሻሻያ እርምጃዎችን ተግባራዊ በማድረግ በኢሰመኮ የዘርፍ ሪፖርቶች የተመላከቱ የሰብአዊ መብቶች ጉዳዮችን እልባት መስጠት ይገባል

Twitter Facebook Telegram Email Whatsapp Download Download Download Download Download Print

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከሰኔ ወር 2016 ዓ.ም. እስከ ሰኔ ወር 2017 ዓ.ም. ያለውን የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች፣ የአካል ጉዳተኞች እና አረጋውያን፣ የሴቶች እና ሕፃናት እንዲሁም የማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መብቶች ሁኔታ የተመለከቱ 4 ዓመታዊ የዘርፍ ሪፖርቶችን ዛሬ ይፋ አድርጓል። ኢሰመኮ ሀገራዊ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታውን ጠቅለል ባለ መልኩ ያቀረበበትን አራተኛውን ዓመታዊ የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ሪፖርት ሐምሌ 28 ቀን 2017 ዓ.ም. ይፋ ማድረጉ የሚታወስ ሲሆን፣ በዛሬው ዕለት ይፋ የተደረጉት 4 የዘርፍ ሪፖርቶች በየዘርፉ ያለውን የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ በተናጠል በዝርዝር የሚያመላክቱ ናቸው።

በዘርፍ ሪፖርቶቹ ውስጥ የተካተቱ ግኝቶች፣ ኢሰመኮ ዓለም አቀፍ፣ አህጉራዊ እና ብሔራዊ የሰብአዊ መብቶች ማዕቀፎችን እንዲሁም የመቋቋሚያ አዋጁን መሠረት በማድረግ በራሱ አነሳሽነት እና በቀረቡለት አቤቱታዎች መነሻነት ባከናወናቸው ልዩ ልዩ ምርመራዎች፣ የሰብአዊ መብቶች ክትትሎች፣ የምክክር መድረኮች፣ ጥናትና ምርምሮች እንዲሁም በሰነዶች ትንተና አማካኝነት ባሰባሰባቸው መረጃዎች እና ማስረጃዎች ላይ የተመሠረቱ ናቸው፡፡ በተጨማሪም ኢሰመኮ የሚጠቀምባቸውን እና በሌሎች ብሔራዊ የሰብአዊ መብቶች ተቋማት እንዲሁም በዓለም አቀፍ አጣሪ ኮሚሽኖች ወይም እውነት አፈላላጊ አካላት ለሰብአዊ መብቶች ምርመራና ክትትል ሥራዎች ጥቅም ላይ የሚውሉ የማስረጃ ምዘና መስፈርቶችን (standard of proof) ያሟሉ ናቸው።

ዓመታዊ የዘርፍ ሪፖርቶቹ በ2017 ዓ.ም. በጀት ዓመት በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች፣ በአካል ጉዳተኞች እና አረጋውያን፣ በሴቶች እና ሕፃናት እንዲሁም በማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መብቶች ረገድ የታዩ ቁልፍ እመርታዎችን፣ አሳሳቢ ሁኔታዎችን እና ምክረ ሐሳቦችን በዝርዝር አካተዋል።

የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ዓመታዊ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ሪፖርት ካመላከታቸው ቁልፍ እመርታዎች መካከል፣ በኅዳር ወር 2017 ዓ.ም. ለሀገር ውስጥ መፈናቀል ዘላቂ መፍትሔ ለማፈለላግ በብሔራዊ ደረጃ እንዲሁም በአፋር፣ አማራ፣ ሶማሊ እና ትግራይ ክልሎች ደረጃ ስትራቴጂዎች መዘጋጀታቸውና አስፈጻሚ የሥራ ቡድኖች መዋቀራቸው፤ እንዲሁም የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች በብሔራዊ የዲጅታል መታወቂያ መርኃ ግብር ተጠቃሚ እንዲሆኑ መደረጋቸው ተጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የተሟላ የሕግ ማዕቀፍ እና በሕግ በግልጽ ሥልጣን የተሰጠው ተቋም አለመኖር ተፈናቃዮች በተራዘመ የመፈናቀል ሁኔታ ውስጥ እንዲቆዩ አስተዋጽዖ ማድረጉ፤ ወቅቱን የጠበቀ፣ ተደራሽ እና ልዩ ፍላጎት ያላቸውን ተፈናቃዮች ያማከለ ሰብአዊ ድጋፍ እንዲሁም ትምህርትና ጤናን ጨምሮ የተሟላ ማኅበራዊ አገልግሎት የማይቀርብ መሆኑና በመጠለያ ጣቢያዎች፣ ተፈናቃዮች በተመለሱባቸው/ አዲስ በሰፈሩባቸው ቦታዎች የተሟላ ጸጥታ እና ደኅንነት ባለመኖሩ ተፈናቃዮች ድጋሚ መፈናቀልን ጨምሮ ለተለያዩ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች መጋለጣቸው በዘርፍ ሪፖርቱ ከተካተቱ አሳሳቢ ጉዳዮች መካከል ናቸው።

የአካል ጉዳተኞችና አረጋውያን መብቶች ሁኔታ ዓመታዊ ሪፖርት በበጀት ዓመቱ ለኢሰመኮ የውትወታ ሥራዎች አዎንታዊ ምላሽ የሰጡ እርምጃዎች በየዘርፉ የተወሰዱ መሆኑን ያመላከተ ሲሆን፣ ለአብነትም  ለአካል ጉዳተኞች እና አረጋውያን መብቶች ጥበቃና መስፋፋት እገዛ የሚያደርጉ አስቻይ የሕግ ማዕቀፎች ዝግጅት እንዲሁም በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በሚገኙ የመንግሥት እና የግል አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የሕንጻ ተደራሽነት ችግሮችን ለማስተካከል እርምጃዎች መወሰዳቸው ተጠቅሰዋል። በአንጻሩ ግጭቶች በቀጠሉባቸው የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚገኙ አካል ጉዳተኞች እና አረጋውያን ላይ ጥቃቶች የሚፈጸሙ መሆኑ፤ በተለይም የአእምሮ እድገት ውስንነት ያለባቸው እና መስማት የተሳናቸው ሰዎች በግጭት ተሳታፊ በሆኑ ኃይሎች የሚደርስባቸው ጥቃት መቀጠሉ እንዲሁም የአረጋውያን እንክብካቤ ማእከላት በግጭቶች ሳቢያ ዐቅማቸው መዳከሙ በሪፖርቱ አሳሳቢ ሆነው ከቀጠሉ ጉዳዮች መካከል ተካተዋል።

የሴቶች እና ሕፃናት መብቶች ሁኔታ ዓመታዊ ሪፖርት ካካተታቸው አበረታች እርምጃዎች መካከል የፍትሕ ሚኒስቴር በሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አተገባበር ሴቶችና ሕፃናትን ጨምሮ የተጎጂዎችና ተጋላጭ የማኀበረሰብ ክፍሎች ተሳትፎ ስትራቴጂን ማርቀቁ፤ የአፋር ክልል ረቂቅ የቤተሰብ ሕግ ድንጋጌዎች ከሰብአዊ መብቶች መርሖች እና መመዘኛዎች ጋር በተጣጣመ መልኩ መሻሻላቸው እንዲሁም በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሴት ልጅ ግርዛት በመፈጸም የተጠረጠሩ ሰዎች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ መደረጉ ይጠቀሳሉ። በሌላ በኩል በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ግርዛትን ጨምሮ በሴቶች እና ሕፃናት ላይ በሚፈጸሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች ሳቢያ በርካታ ሴቶች እና ሕፃናት ለተለያዩ ውስብስብ የጤና ጉዳቶች እንዲሁም ማኅበራዊ፣ ሥነ-ልቦናዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጫናዎች እየተዳረጉ መቀጠላቸው እንዲሁም የፍትሕ እና የአንድ ማእከል አገልግሎት ተቋማት የቋንቋ፣ አካላዊና የመረጃ ተደራሽነት ችግር ያሉባቸው በመሆኑ ምክንያት በወንጀል ፍትሕ ሥርዓት ውስጥ የሚያልፉ የጥቃት ተጎጂ ሴቶች እና ሕፃናት ለዘርፈ ብዙ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችና ሥጋቶች የተጋለጡ መሆናቸው ተመላክቷል።

በበጀት ዓመቱ ጸድቀው ሥራ ላይ የዋሉ የጤና አገልግሎት፣ የትምህርት፣ የንብረት ታክስ እና የሕንጻ አዋጆች ለተለያዩ ሰብአዊ መብቶች ዝርዝር ዕውቅና ከመስጠት በተጨማሪ፣ የአካል ጉዳተኞች፣ አረጋውያን፣ ሕፃናት እና ሴቶችን ጨምሮ የተጋላጭ የማኅበረሰብ ክፍሎች መብቶች ጥበቃን የሚያጠናክሩ መሆናቸው እንዲሁም የንግድ እና ሰብአዊ መብቶች ብሔራዊ የድርጊት መርኃ ግብር ዝግጅት ተጠናክሮ መቀጠሉ በማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መብቶች ሁኔታ ዓመታዊ ሪፖርት ተገልጿል። ግጭቶች በቀጠሉባቸው አካባቢዎች ብዙ ቁጥር ያላቸው የጤና እና የትምህርት ተቋማት በመውደማቸው አገልግሎት መስጠት ማቆማቸውና በዚህም በርካታ ሕፃናት ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸው፣ በተለያዩ አካባቢዎች በተከሰቱ የወባ፣ ኮሌራና ኩፍኝ ወረርሽኞች ብዙ ሰዎች ተጎጂ መሆናቸው እንዲሁም የሠራተኞች ደመወዝ በወቅቱና በአግባቡ ባለመከፈሉ ምክንያት ሠራተኞች ለተለያዩ ችግሮች መዳረጋቸው በአሳሳቢነት ከተገለጹ ጉዳዮች መካከል ናቸው።

ኢሰመኮ ይፋ ያደረጋቸው የዘርፍ ሪፖርቶች ግኝቶችን መሠረት ያደረጉ ዝርዝር ምክረ ሐሳቦችን በማቅረብ፣ አበረታች ሁኔታዎች ተጠናክረው የሚቀጥሉበትን እንዲሁም አሳሳቢ ጉዳዮች ፈጣን፣ ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ መፍትሔ የሚያገኙበትን መንገድ የሚያመላክቱ ናቸው።

የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ ኢሰመኮ ይፋ ያደረጋቸው የዘርፍ ሪፖርቶች ሀገራዊ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታውን በጉልህ ማሳያዎች አማካኝነት በዝርዝር የሰነዱ መሆናቸውን አንስተው፤ የፖሊሲ፣ የሕግና የአሠራር ማሻሻያ እርምጃዎችን ተግባራዊ በማድረግ በሪፖርቶቹ የተመላከቱ የሰብአዊ መብቶች ጉዳዮችን እልባት መስጠት እንደሚገባ ገልጸዋል። በተለይም መንግሥት ሰብአዊ መብቶችን የማክበር፣ የማስከበር (የመጠበቅ) እና የማሟላት ባለግዴታ መሆኑን በመጥቀስ፣ ኢሰመኮ በፌዴራልና በክልል መንግሥታት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ደረጃ የጀመራቸውን የውትወታ ተግባራት አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። አክለውም፣ በሂደት ላይ የሚገኙት የሽግግር ፍትሕ እና የሀገራዊ ምክክር ጥረቶች በኢሰመኮ ሪፖርቶችና የውትወታ መድረኮች አማካኝነት በተደጋጋሚ የሚነሱ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችን፣ ሥጋቶችን እና መነሻ ምክንያቶችን በዘላቂነት መፍትሔ ለመስጠት በሚችሉበት አግባብ መከናወናቸውን ማረጋገጥ እንደሚገባ ገልጸው፣ ለዚህም ሁሉም ባለድርሻ አካላት በትኩረት ሊሠሩ ይገባል ብለዋል።

የአካል ጉዳተኞች እና አረጋውያን መብቶች ሁኔታ ዓመታዊ ሪፖርት
የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ዓመታዊ ሪፖርት
የማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ መብቶች ሁኔታ ዓመታዊ ሪፖርት
የሴቶች እና የሕፃናት ሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ዓመታዊ ሪፖርት

Related posts

November 6, 2024January 23, 2025 Press Release
የአካል ጉዳተኞች እና አረጋውያን ሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ዓመታዊ ሪፖርት
September 6, 2023September 6, 2023 Press Release
የአካል ጉዳተኞች እና አረጋውያን መብቶችን በተመለከተ አስቻይ የሕግ እና ተቋማዊ ማእቀፎች ሊቀረጹ ይገባል
May 23, 2023August 28, 2023 EHRC Quote
በአዲስ አበባ ከተማ የንግድ ቤቶችን ከማፍረስ ሂደት ጋር በተያያዘ አካል ጉዳተኞች ለኢሰመኮ ያቀረቡትን አቤቱታ በተመለከተ
October 25, 2024October 28, 2024 Press Release
የሴቶች እና የሕፃናት ሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ዓመታዊ ሪፖርት

Signup for the Latest Update from EHRC

Submit your email to singup
Facebook Like us on FacebookXFollow us on XYouTube Follow us on YouTubeLinkedin Follow us on LinkedinWhatsApp WhatsAppTikTok TikTokTelegram TelegramInstagram InstagramFlicker Flickr

Useful Links

  • NANHRI
  • GANHRI
  • OHCHR
  • ACHPR

Get Involved

  • Jobs
  • Events
  • Contact Us
  • Telegram Bot
  • Subscribe to our newsletter

Connect with Us

  • Facebook
  • Twitter
  • LinkedIn
  • YouTube
  • Flickr
  • Instagram
Descriptive Text

We are an independent
national human rights
institution tasked with
the promotion and protection of human
rights in Ethiopia.

Submit your email to get the latest update from EHRC

Address: Sunshine Tower No. 5, Meskel Square, on Bole Road next to Hyatt Regency Hotel, Addis Ababa, Ethiopia
Tel: +251115504031 | Fax: +251 11 550 4125 | PO Box 1165 Addis Ababa | Email: info@ehrc.org


The contents of this website, excepting third party content for which the Commission bears no responsibility,
may be freely used and copied for educational and other non-commercial purposes, provided that any such reproduction is accompanied by an acknowledgement of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC). Source of images used in the content of this website: EHRC Media and Communications Department Archive and Creative Common License.

This website is managed by the Media and Communications team of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC).

Accessibility Adjustments

Powered by OneTap

How long do you want to hide the toolbar?
Hide Toolbar Duration
Select your accessibility profile
Vision Impaired Mode
Enhances website's visuals
Seizure Safe Profile
Clear flashes & reduces color
ADHD Friendly Mode
Focused browsing, distraction-free
Blindness Mode
Reduces distractions, improves focus
Epilepsy Safe Mode
Dims colors and stops blinking
Content Modules
Font Size

Default

Line Height

Default

Color Modules
Orientation Modules

We are using cookies to give you the best experience on our website.

You can find out more about which cookies we are using or switch them off in .

Scroll to top
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
    • Addis Ababa
    • Afar
    • Amhara
    • Benishangul Gumuz
    • Gambella
    • Oromia
    • Somali
    • SNNP (formerly)
    • Tigray
  • Areas of Work
    • Economic, Social & Cultural Rights
    • Civil & Political Rights
    • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
    • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
    • Women’s & Children’s Rights
    • HR Monitoring & Investigation
    • Human Rights Education
    • Human Rights Film Festival
    • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Videos
    • Newsletters
    • EHRC Visuals
    • Events
  • The Latest
    • Expert View
    • Explainer
    • Event Update
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Report (June 2024 – June 2025)
  • Resources
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Search
Ethiopian Human Rights Commission - EHRC
Powered by  GDPR Cookie Compliance
Privacy Overview

This website uses cookies so that we can provide you with the best user experience possible. Cookie information is stored in your browser and performs functions such as recognising you when you return to our website and helping our team to understand which sections of the website you find most interesting and useful.

Strictly Necessary Cookies

Strictly Necessary Cookie should be enabled at all times so that we can save your preferences for cookie settings.