የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በአማራ ክልል ከመስከረም ወር አጋማሽ 2017 ዓ.ም. ጀምሮ በአዲስ መልክ ጎንደር እና ባሕር ዳር ከተሞችን ጨምሮ በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች የሚፈጸመውን የበርካታ ሰዎች እስር በተመለከተ ክትትል ማድረጉን የሚቀጥል ሲሆን፣ በማናቸውም ወቅት ቢሆን የሚፈጸም እስር ተገቢውን የሕግ እና የሰብአዊ መብቶች ድንጋጌዎች ሊከተል የሚገባ መሆኑን ያሳስባል
በትጥቅ ግጭት እና በጸጥታ መደፍረስ ወቅትም ቢሆን ሲቪል ሰዎችን በቁጥጥር ሥር ለማዋል የሚያበቃ በቂ ሕጋዊ ምክንያት መኖሩን ማረጋገጥ ያስፈልጋል
Event update - Peer to peer learning between regional victims’ associations and collectives (1) Participants held collaborative discussions on establishing a consortium for victims’ associations addressing key issues related to forming and operating the consortium, aiming to enhance collaboration and strengthen their role in the national transitional justice process
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሴቶች፣ የሕፃናት፣ የአካል ጉዳተኞች እና የአረጋውያን መብቶች ኮሚሽነር ርግበ ገብረሐዋሪያ፣ በጾታ ዕኩልነት ላይ በአማካሪነት የሚሠሩት ወይዘሮ አሻም አሳዝነው፤ የጾታ ዕኩልነት አዶቮኬት የሆኑት ርብቃ ዳዊት እና ረዳት ፕሮፌሰር ሱራፌል ወንድሙ በውይይቱ ተሳትፈዋል
በተጠርጣሪዎች ሰብአዊ መብቶች አያያዝ ረገድ ያሉ ክፍተቶችን ለማረም ተጠያቂነትን የማረጋገጥ እና አሠራሮችን የማሻሻል ተግባራትን ማጠናከር ያስፈልጋል
የሽግግር ፍትሕ ሂደቱ እና ሀገራዊ የምክክር መድረኩ ለማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መብቶች በቂ ትኩረት በሚሰጥ መልኩ ተግባራዊ እንዲሆን ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን አስተዋጽዖ ሊያደርጉ ይገባል
ኢሰመኮ የሰዎች እገታ እየተበራከት ነው አለ
ኢሰመኮ በዚህ መግለጫው የእገታ ጉዳዮች ለማሳያነት አቅርቧል
ታጣቂዎች የሚፈጽሟቸው የእገታ ተግባራት ከዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ድንጋጌዎች ጋር የሚቃረን በመሆኑ ከድርጊታቸው መቆጠብ እንደሚኖርባቸው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አስታውቋል
የአካል ጉዳተኛ ተማሪዎችን የትምህርት መብት ለማረጋገጥ የመምህራንን ግንዛቤ በማዳበር የትምህርት አሰጣጡ ሰብአዊ መብቶችን መሠረት ያደረገ እንዲሆን ማስቻል ይገባል