በኢትዮጵያ በተለያዩ ክልሎች ባሉ ግጭቶች እና በሌሎችም ምክንያቶች የተነሳ ከ5500 በላይ ትምህርት ቤቶች የመማር ማስተማር ሥራቸውን ከማከናወን ውጪ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ገለጸ
ኢሰመኮ ትኩረት ሰጥቶ ከሚሠራባቸው የሰብአዊ መብቶች ዘርፎች መካከል በፖሊስ ጣቢያዎች እና በማረሚያ ቤቶች የሚገኙ ታራሚዎችን የሰብአዊ መብቶች ጥሰትን በተመለከተ የመከታተልና ጉዳዩ እልባት እንዲያገኝ ከሚመለከተው አካል ጋር እየተነጋገሩ እንደሆነ ከተቋሙ ባገኘነው መረጃ ለማወቅ ተችሏል
በተለይም ግጭት ባለባቸው በኦሮሚያ፣ አማራ እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች በታጣቂዎች በሚፈጸም ጥቃት እና መንግሥት ያንን ለመከላከል አልያም ለፍትሕ ለማቅረብ በሚደርገው እንቅስቃሴ ውስጥ ንፁሐን እየሞቱ እና እየተጎዱ መሆኑን መንግሥታዊው የሰብአዊ መብቶች ተቆርቋሪው ኢሰመኮ ተናግሯል
በ2016 ዓ.ም. በበርካታ የኢትዮጵያ አከባቢዎች በተለምዶ ወቅታዊ ሁኔታ በሚል ምክንያቶች ሳቢያ ሰዎች ለዘፈቀደ እስር እንዲሁም ለአስገድዶ መሰወር የተዳረጉበት በርካታ ክስተቶች መመዝገቡን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን አስታወቀ
ኮሚሽኑ ከሰኔ ወር 2015 ዓ.ም. እስከ ሰኔ ወር 2016 ዓ.ም. ያለውን ጊዜ የሚሸፍነው 3ኛው የኢትዮጵያ ዓመታዊ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ሪፖርት ይፋ አድርጓል
የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች በቂ እና ወቅቱን የጠበቀ የምግብ ድጋፍ እየቀረበላቸው ባለመሆኑ ለረሀብ አደጋ እየተጋለጡ ናቸው
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፀጥታ ጥበቃና ከገጽታ ግንባታ ጋር በተያያዘ ምክንያት የንግድ ቦታቸው የፈረሰባቸው አካል ጉዳተኞች፣ ለልመና ወደ አደባባይ መውጣታቸውን፣ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አስታወቀ
The Ethiopian Human Rights Commission (EHRC) has urged the government to address the urgent needs of people with disabilities who have lost their business establishments due to there recent wave of demolitions in the city. This appeal follows the 2023 dismantling of small trading businesses by the city administration, which has left many disabled business owners without their means of livelihood
አደጋውን በተመለከተ ማብራሪያ የሰጠው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን በዞኑ የደረሰው አደጋ በዜጎች ሕይወት ፣ በመኖሪያ ቤቶችና እና በስራ ቦታዎች ላይ ከፍተና ጉዳት ማድረሱን ገልቷል
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ ጎፋ ዞን፣ በገዜ ጎፋ ወረዳ በኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ ሐምሌ 14 ቀን 2016 ዓ.ም. ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት አካባቢ የደረሰው የመሬት ናዳ አደጋን ተከትሎ በሰዎች ሕይወት ላይ፣ በመኖሪያዎቻቸው እና በመተዳደሪያዎቻቸው ላይ የደረሰውን ጉዳት በተመለከተ የሚደርሱት ጥቆማዎች እና ሪፖርቶች በእጅጉ አሳሳቢ ናቸው ብሏል