Skip to content
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Ethiopian Human Rights Commission – EHRC
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
        • Regions

          EHRC is an independent federal institution tasked with the promotion and protection of human rights in Ethiopia.

        • Addis Ababa
        • Afar
        • Amhara
        • Benishangul Gumuz
        • Gambella
        • Oromia
        • Somali
        • Tigray
        • Central Ethiopia
        • Dire Dawa
        • Harari
        • Sidama
        • South Ethiopia
        • South West Ethiopia Peoples'
  • Areas of Work
        • Areas of Work

          We are an independent national human rights institution tasked with the promotion & protection of human rights in Ethiopia.

        • Economic, Social & Cultural Rights
        • Civil & Political Rights
        • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
        • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
        • Women’s & Children’s Rights
        • Human Rights Education
        • Human Rights Monitoring & Investigation
        • Human Rights Film Festival
        • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
 
Ethiopian Human Rights Commission – EHRCEthiopian Human Rights Commission – EHRC

የትጥቅ ግጭቶች ለሰብአዊ መብቶች ጥሰት ዋነኛ ምክንያት ሆነው በመቀጠላቸው ግልጽ፣ አካታች እና ተዓማኒ የሆነ ሰላማዊ መፍትሔ እና የሽግግር ፍትሕ ሂደት አፋጣኝ አስፈላጊነት አመላካች ነው

July 5, 2024November 19, 2024 Press Release, Report

የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ የሥራ ዘመናቸው ማብቃት ጋር በተገጣጠመው በዚህ በ3ተኛው የኢትዮጵያ ዓመታዊ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ሪፖርት ባስተላለፉት መልእክት፡ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከግጭት ለመውጣትና መጠነ ሰፊ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችን በዘላቂነት ለመፍታት ሰላማዊ ውይይት እና ምክክር ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል

Twitter Facebook Telegram Email Whatsapp Download Download Download Download Download Print

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከሰኔ ወር 2015 ዓ.ም. እስከ ሰኔ ወር 2016 ዓ.ም. ያለውን ጊዜ የሚሸፍነውን 3ተኛው የኢትዮጵያ ዓመታዊ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ባለ 132 ገጽ ሪፖርት ዛሬ ይፋ አድርጓል፡፡ ሪፖርቱ በበጀት ዓመቱ በተሰበሰቡ መረጃ እና ማስረጃዎች መሠረት ሀገራዊ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታን ጠቅለል ባለ መልኩ የሚያሳይ ሲሆን፣ መልካም እመርታዎች፣ አሳሳቢ ጉዳዮች፣ ምክረ ሐሳቦች እና በቀጣይ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮችንም በዝርዝር አካቷል። 

ዓመታዊ ሪፖርቱ ኢሰመኮ የትኩረት መስክ አድርጎ በለያቸው የሲቪልና የፖለቲካ፣ የማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ፣ የሴቶችና ሕፃናት፣ የአካል ጉዳተኞችና አረጋውያን፣ የስደተኞች፣ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች እና ፍልሰተኞች መብቶች ዘርፎችን የተመለከተ ሲሆን፤ በተጨማሪም ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 6/2015 አተገባበር ጋር ያለውን የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ፣ በጥበቃ ሥር ያሉ ሰዎች እና የታራሚዎች የሰብአዊ መብቶች አያያዝ ሁኔታን፣ በ4 ክልሎች የተካሄደውን የ6ኛው ዙር ቀሪ እና ድጋሚ ምርጫ የሰብአዊ መብቶች ክትትል፣ በኢሰመኮ የተስተናገዱ የሰብአዊ መብቶች ጉዳይ አቤቱታዎች እና አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ የሰብአዊ መብቶች ግዴታዎችን ከመወጣት አንጻር ኢትዮጵያ ያለችበት ሁኔታንም በዝርዝር አብራርቷል።  

በሪፖርት ዘመኑ ከተመዘገቡ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታን ማሻሻል ከሚያስችሉ ቁልፍ ክስተቶች እና እመርታዎች መካከል የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ መጽደቁ በዋነኝነት የሚጠቀስ መሆኑን አስታውሶ፤ ከታጠቁ ኃይሎች ጋር የተጀመሩ ሰላምን የማምጣት እንቅስቃሴዎች አበረታች ቢሆኑም ዘላቂ እንዲሆኑ ሂደታቸው ተጎጂዎችን ጨምሮ ሁሉንም ባለድርሻ አካላት ያካተቱ እና ግልጽ ሊሆኑ እንደሚገባ፤ የተጀመረውም የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አጠቃላይ ሂደት ተጎጂዎችን ማእከል ያደረገ፣ ተዓማኒ እና ግልጽነት ያለው፣ እንዲሁም ዓለም አቀፍ መስፈርቶችን ያሟላ እና የሰብአዊ መብቶች መርሖችን የተከተለ እንዲሆን ከፍተኛ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ በሪፖርቱ ተመላክቷል። 

በአብዛኛው የኢትዮጵያ ክልሎች የትጥቅ ግጭቶች፣ ጥቃቶች ወይም የጸጥታ መደፍረሶች ከሐምሌ 1 ቀን 2015 ዓ.ም. እስከ ግንቦት ወር 2016 ዓ.ም. የተመዘገቡ ሲሆን፣ በዚህ ሳቢያ በታጣቂ ኃይሎች እና በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በተወሰዱ እርምጃዎች በሲቪል ሰዎች ላይ የሚደርስ የሞት እና የአካል ጉዳት አሳሳቢነት ቀጥሏል። በተለይም በትጥቅ ግጭት ዐውድ ውስጥ በሲቪል ሰዎች ላይ የሚደርሱ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች እንደቀጠሉ እና እንደተስፋፉ በሪፖርቱ ተመላክቷል። የትጥቅ ግጭት በሚካሄድባቸው አካባቢዎች ተጠልለው የሚገኙ ተፈናቃዮች፣ በተለይም ሴቶችና ሕፃናት፣ አካል ጉዳተኞችና አረጋውያን ለምግብና ለመሠረታዊ ሰብአዊ ድጋፍ እጥረት፣ ለጤና እና ትምህርት አገልግሎቶች መስተጓጎል ወይም መቋረጥ እንዲሁም ለሌሎች ተጨማሪ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ተጋላጭ መሆናቸውም ተገልጿል። 

በሪፖርት ዘመኑ በትጥቅ ግጭት፣ በግጭት ውስጥ በቆዩ አካባቢዎች እንዲሁም ግጭት በሌለበት በአንዳንድ ሁኔታዎች ወቅት ጭምር የሚፈጸም ከሕግ ውጪ የሆኑ የሲቪል ሰዎች ግድያ አሳሳቢ ሆኖ ቀጥሏል። በአማራ እና በኦሮሚያ ክልል በሲቪል ሰዎች ላይ በትጥቅ ግጭቱ እንዲሁም በግጭቱ ዐውድ ውስጥ ከሚደርሱ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች በተጨማሪ ሲቪል ሰዎችን ዒላማ ያደረገ እገታ አሳሳቢነት ከፍተኛ ትኩረት የሚሻ ጉዳይ መሆኑ በሪፖርቱ ተመላክቷል። 

ኢሰመኮ በበጀት ዓመቱ ለ10 ወራት ተፈጻሚ ሆኖ የቆየው የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ አዋጅ አተገባበር ጋር ያለውን የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ክትትል ሲያደርግ መቆየቱን፤ በዚህ ሁኔታ ውስጥ በርካታ ሰዎች መደበኛ እና መደበኛ ባልሆኑ ማቆያ ቦታዎች ውስጥ ለተራዘመ እስር መዳረጋቸውን፤ እንዲሁም ለቀናት ወይንም ለሳምንታት ለቆየ ጊዜ ያሉበት ቦታ ሳይገለጽ/ሳይታወቅ በእስር መቆየተቻው ተገልጿል። ኢሰመኮ ሁሉንም መደበኛ ያልሆኑ ቦታዎችን በመጎብኘት ክትትል እና ምርመራ ለማድረግ ያደረገው ጥረት ባይሳካም፣ የደረሱትን አቤቱታዎችና ጥቆማዎች መሠረት በማድረግ ከሚመከለታቸው የክልል እና የፌዴራል የአስተዳደርና የጸጥታ አካላት ጋር በመነጋገርና ውትወታ በማድረግ ሲከታተል መቆየቱን፤ እንዲሁም ያሰባሰባቸውን ማስረጃዎች መሠረት በማድረግ በተለያየ ወቅት መግለጫዎችን ይፋ ማድረጉ በሪፖርቱ ተመልክቷል።  

ከአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ አዋጁ አተገባበር ጋር ተያይዞ ከኮማንድ ፖስቱ ትዕዛዝ ውጪ በተለይ በአዲስ አበባ ከተማ፣ በአማራ፣ በኦሮሚያ፣ በሲዳማ፣ በማእከላዊ ኢትዮጵያ እና በደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎች የሚዲያ እና የፖለቲካ ፓርቲ አባላትን ጨምሮ በርካታ ሰዎች ለእስር መዳረጋቸውን በዚህ ዝርዝር ሪፖርት ተመላክቷል።  

በሌላ በኩል “ወቅታዊ ሁኔታ” በሚል ምክንያት ሰዎች ለዘፈቀደ እስር እንዲሁም ለአስገድዶ መሰወር የተዳረጉበት በርካታ ክስተቶች በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች መመዝገባቸውን፣ የመንቀሳቀስ መብትን በተመለከተ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ባለው የጸጥታ ሁኔታ ወይም በሚጣሉ ገደቦች ምክንያት በተለይም በየብስ የሚደረግን እንቅስቃሴ አዳጋች ማድረጉ፤ እንዲሁም የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች ወይም በታጣቂ ቡድኖች ለተከታታይ ቀናት በሚዘጉ መንገዶች ምክንያት የሚደርሱ ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ ችግሮች፣ በሸቀጦች ዋጋ እና በገቢ እንዲሁም በጤና እና ትምህርት አገልግሎቶች ተደራሽነት ላይ የሚደርሱ አሉታዊ ተጽዕኖዎች በዘንድሮ በጀት ዓመትም በተለይ በአማራ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ በጋምቤላ እና በኦሮሚያ ክልሎችም መቀጠላቸው በዝርዝር ተብራርቷል።  

ኢሰመኮ በበጀት ዓመቱ በአጠቃላይ 306 ፖሊስ ጣቢያዎችን እና 52 ማረሚያ ቤቶችን እንዲሁም አዋሽ አርባን ጨምሮ 15 መደበኛ ያልሆኑ ማቆያ ቦታዎችን ጎብኝቷል። ክትትል በተደረገባቸው ፖሊስ ጣቢያዎች እና ማረሚያ ቤቶች በርካታ መሻሻሎች ተስተውለዋል። ሆኖም በሁሉም ክልሎች ለማለት በሚያስችል ሁኔታ የዘፈቀደ እስር፣ የጅምላ እስር ወይም የፍርድ ቤት ውሳኔዎችን ባለማክበር ሰዎችን ይዞ የማቆየት፣ መደበኛ ባልሆኑ ማቆያ ቦታዎች ሰዎችን የመያዝ ድርጊቶች ተፈጽመዋል።  

የተፈናቃዮች ሰብአዊ መብቶች ሁኔታን በተመለከተ በመንግሥት እንዲሁም መንግሥታዊ ባልሆኑ ተቋማት የሰብአዊ ድጋፍ በተለይ የምግብ ድጋፍ ለማቅረብ የሚደረገው ጥረት፤ በተወሰኑ የተፈናቃይ መጠለያ ጣቢያዎች በየጊዜው ወቅታዊ የሚደረግ የተሰባጠረ የተፈናቃዮች የመረጃ አያያዝ ሥርዓት መኖሩ፤ የስደተኞች እና ጥገኝነት ጠያቂዎች መብቶችን በተመለከተ የተለያዩ ዓለም አቀፍ እና ሀገር በቀል የተራድዖ ድርጅቶች መንግሥት ለስደተኞች እና ጥገኝነት ጠያቂዎች የሚያደርገው ጥበቃ እና ድጋፍ የተሟላ እንዲሆን ድጋፍ የሚያደርጉ መሆኑ በበጀት ዓመቱ ከታዩ መልካም እመርታዎች መካከል ናቸው። ሆኖም በሀገር አቀፍ ደረጃ የተፈናቃዮች ምዝገባ እና ሰነድ አሰጣጥ ሂደቱ ላይ ያለው ክፍተት መቀጠሉ፤ ለተፈናቃዮች የሚደረገው ድጋፍ በአግባቡ እንዳይከናወን አሉታዊ ተጽዕኖ ከማሳደሩ በተጨማሪ ሌሎች የመንቀሳቀስ እና የማኅበራዊ አገልግሎት የማግኘት መብቶቻቸውን ለመጠቀም እንዳይችሉ እንቅፋት መፍጠሩ እንደቀጠለ ነው።  

ወቅቱን የጠበቀ፣ በቂ፣ ያልተቆራረጠ እንዲሁም ልዩ ፍላጎቶች ያሏቸውን ተፈናቃዮች መሠረት ያደረገ የሰብአዊ ድጋፍ እና ማኅበራዊ አገልግሎቶች አቅርቦት አለመኖሩ፤ በሀገሪቱ በተለያዩ አካባቢዎች ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ በሆኑ ምክያቶች በመፈናቀል ሁኔታ ውስጥ ያሉ የሴቶች፣ ሕፃናት፣ አካል ጉዳተኞች እና አረጋውያን የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ እጅግ አሳሳቢ መሆኑ፤ በትጥቅ ግጭት ዐውድ ውስጥ ባሉ አካባቢዎች በሴቶች እና ሕፃናት ላይ የሚደርሱ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች በተለይም ወሲባዊ እና ጾታዊ ጥቃት መጨመሩ በዓመታዊ ሪፖርቱ ከተነሱ አሳሳቢ ጉዳዮች መካከል ናቸው። 

በመጪው በጀት ዓመት ትኩረት ከሚሹ አንኳር ጉዳዮች መካከል የትጥቅ ግጭቶች በሰላማዊ ውይይት እንዲፈቱ ማድረግ፣ የሀገራዊ ምክክር እና የሽግግር ፍትሕ ሂደት ተዓማኒ አተገባበር ማረጋገጥ፣ ከፍርድ ቤት ትእዛዝ ውጪ በእስር ላይ የሚገኙ ሰዎች ሁሉ በአፋጣኝ እንዲለቀቁ ወይም የዋስትና መብታቸው እንዲከበር ማድረግ፤ በሰብአዊ መብቶች ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ በሚያሳድሩ ሕግ እና ፖሊሲዎች ላይ ማሻሻያ ማድረግ፤ በጥበቃ ሥር ያሉ ሰዎች እና የታራሚዎች የሰብአዊ መብቶች አያያዝ ማሻሻልና ማረጋገጥ፣ የትጥቅ ግጭቶች በኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ መብቶች ላይ ያሳደሩት አሉታዊ ተጽዕኖ፣ እንዲሁም የመንግሥት የፋይናንስና የበጀት እጥረት በተለይም በጤና እና በትምህርት አገልግሎቶች ላይ ያስከተለው ጉዳት ታሳቢ በማድረግ በኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ መብቶች ዘርፍ የሚከናወነውን ሥራ ማጠናከርና ማጎልበት የሚሉት ተጠቃሽ ናቸው። 

የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ የሥራ ዘመናቸው ማብቃት ጋር በተገጣጠመው በዚህ በ3ተኛው የኢትዮጵያ ዓመታዊ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ሪፖርት ባስተላለፉት መልእክት፣ “ኢትዮጵያ ከምትገኝበት የግጭት አዙሪት ዐውድ ለመውጣትና በዚሁ ዐውድ ለደረሱ መጠነ ሰፊ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች በዘላቂነት እልባት ለመስጠት ከሰላማዊ መንገድ፣ ከውይይት፣ ከምክክር እና ከሽግግር ፍትሕ ሂደት ውጪ ሌላ አማራጭ የለም” ብለዋል። አክለውም የሽግግር ፍትሕ ሂደት ተዓማኒና ቅቡልነት ባለው መንገድ ለመተግበር መንግሥትን ጨምሮ ሁሉም ባለድርሻ አካላት፣ በሀገሪቱ በተለያዩ ክፍሎች በሚካሄዱ የትጥቅ ግጭቶች ተሳታፊ የሆኑ ወገኖች፣ እንዲሁም የሀገሪቱ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ይመለከተኛል የሚሉ ሁሉም ወገኖች፤ ለሀገራዊ ምክክሩና ለሽግግር ፍትሕ ሂደቱ በቀና መንፈስ ዕድል እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል። 

. . . 

Click here for the English version

የኢትዮጵያ ዓመታዊ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ሪፖርት
አንኳር ጉዳዮች:- የኢትዮጵያ ዓመታዊ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ሪፖርት
Annual Ethiopia Human Rights Situation Report
Executive Summary: Annual Ethiopia Human Rights Situation Report
ኢሰመኮ ከ 2012 እስከ 2016 ዓ.ም. ያስመዘገባቸው ውጤቶች አጭር ገለጻ

Related posts

February 13, 2024February 13, 2024 Press Release
በአማራ ክልል አሳሳቢነቱ የቀጠለው የትጥቅ ግጭት እና በሲቪል ሰዎች ላይ ከሕግ ውጭ የተፈጸሙ ግድያዎች (Extra-judicial killings)
April 12, 2023April 12, 2023 Press Release
መንግሥት የክልል ልዩ ኃይሎችን መልሶ የማደራጀትን ውሳኔ ትግበራ በውይይትና የሰዎችን ሰብአዊ መብቶች አደጋ ላይ በማይጥል ሁኔታ ሊከውን ይገባል
October 30, 2024October 30, 2024 Press Release
የማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ መብቶች ሁኔታ ዓመታዊ ሪፖርት
August 4, 2023August 28, 2023 Press Release
በአማራ ክልል ያለውን አሳሳቢ የጸጥታ ሁኔታ በተመለከተ

Signup for the Latest Update from EHRC

Submit your email to singup
Facebook Like us on FacebookXFollow us on XYouTube Follow us on YouTubeLinkedin Follow us on LinkedinWhatsApp WhatsAppTikTok TikTokTelegram TelegramInstagram InstagramFlicker Flickr

Useful Links

  • NANHRI
  • GANHRI
  • OHCHR
  • ACHPR
  • TRANSITIONAL JUSTICE

Get Involved

  • Jobs
  • Events
  • Contact Us
  • Telegram Bot
  • Subscribe to our newsletter

Connect with Us

  • Facebook
  • Twitter
  • LinkedIn
  • YouTube
  • Flickr
  • Instagram
Descriptive Text

We are an independent
national human rights
institution tasked with
the promotion and protection of human
rights in Ethiopia.

Submit your email to get the latest update from EHRC

Address: Sunshine Tower No. 5, Meskel Square, on Bole Road next to Hyatt Regency Hotel, Addis Ababa, Ethiopia
Tel: +251115504031 | Fax: +251 11 550 4125 | PO Box 1165 Addis Ababa | Email: info@ehrc.org


The contents of this website, excepting third party content for which the Commission bears no responsibility,
may be freely used and copied for educational and other non-commercial purposes, provided that any such reproduction is accompanied by an acknowledgement of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC). Source of images used in the content of this website: EHRC Media and Communications Department Archive and Creative Common License.

This website is managed by the Media and Communications team of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC).

We are using cookies to give you the best experience on our website.

You can find out more about which cookies we are using or switch them off in .

Scroll to top
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
    • Addis Ababa
    • Afar
    • Amhara
    • Benishangul Gumuz
    • Central Ethiopia
    • Dire Dawa
    • Gambella
    • Harari
    • Oromia
    • Sidama
    • Somali
    • South Ethiopia
    • South West Ethiopia Peoples’
    • Tigray
  • Areas of Work
    • Economic, Social & Cultural Rights
    • Civil & Political Rights
    • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
    • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
    • Human Rights Monitoring & Investigation
    • Women’s & Children’s Rights
    • Human Rights Education
    • Human Rights Film Festival
    • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Search
Ethiopian Human Rights Commission - EHRC
Powered by  GDPR Cookie Compliance
Privacy Overview

This website uses cookies so that we can provide you with the best user experience possible. Cookie information is stored in your browser and performs functions such as recognising you when you return to our website and helping our team to understand which sections of the website you find most interesting and useful.

Strictly Necessary Cookies

Strictly Necessary Cookie should be enabled at all times so that we can save your preferences for cookie settings.

If you disable this cookie, we will not be able to save your preferences. This means that every time you visit this website you will need to enable or disable cookies again.