Everyone has the right to education. Primary education shall be compulsory and available free to all
ማንኛውም ሰው የመማር መብት አለው። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት መማር ግዴታ ሊሆንና ለሁሉም ሰው በነጻ ሊሰጥ ይገባል
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በተለይ በአፍሪካ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚታሰበውን እና በየዓመቱ እ.ኤ.አ. ሰኔ 30 የሚውለውን የአፍሪካ ሳይንሳዊ ሕዳሴ ቀን (Africa Scientific Renaissance)፣ እንዲሁም የዓመቱ የትምህርት ወቅት መዝጊያን በማስመልከት በተዘጋጀ ማብራሪያ ትምህርት መሠረታዊ የሰብአዊ መብት መሆኑን በማስታወስ፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ በግጭት፣ በመፈናቀል፣ በአካል ጉዳት፣ በመሠረተ ልማት ውድመት፣ እንዲሁም በኑሮ ውድነት እና ሌሎች ምክንያቶች ከትምህርት ውጪ ሆነው ለበርካታ ወራት የቆዩ ሕፃናትን በ2016 ዓ.ም. ወደ ትምህርት እንዲመለሱ የማድረጉ ሥራ ከፍተኛ እና የተቀናጀ ትኩረት እንዲሰጠው ጥሪ ያቀርባል።
ተማሪዎቹ አገልግሎት በሚያገኙባቸው ቢሮዎች ፣ በትምህርት እና መልዕክት ማስተላለፊያ መንገዶች እና በሌሎች የመብት ጥሰት ይደርስባቸዋል ተብሏል
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች በአምስቱ ላይ ባደረገው ክትትል፣ ሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች የአካል ጉዳተኛ ተማሪዎች ጉዳይ የሚመራበት የጽሑፍ ፖሊሲ እንደሌላቸው ማረጋገጡን አስታወቀ
ሰብአዊ መብቶች ባህል የሆኑባት ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በሰብአዊ መብቶች መርሖች እና እሴቶች የታነጸ ትውልድ ማፍራት አስፈላጊ ነው
ስልጠናዎቹ ሰብአዊ መብቶችን እና የሰብአዊ መብቶች እሴቶችን መሠረት በማድረግ የሰልጣኞችን ዕውቀት፣ ክህሎት እና አመለካከት ለመገንባት ያለሙ ናቸው
በክልል ውድድሮች ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ስምንት ትምህርት ቤቶች ከግንቦት 12 እስከ 19 ቀን 2015 ዓ.ም. በሚካሄደው ሀገራዊ ውድድር ተሳታፊ ይሆናሉ
በመፈናቀል ምክንያት ከትምህርት ገበታ ውጪ የሆኑ ሕፃናት የትምህርት አገልግሎት እንዲያገኙ እና ወደ መደበኛ የትምህርት ሥርዓት እንዲመለሱ የሁሉንም ጥረት ይፈልጋል
States Parties shall take specific positive action to promote literacy among women