ተጠያቂነትን ለማስፈን፣ እውነትን ለማውጣት፣ ማኅበረሰባዊ እርቅ እና ፈውስ ለማምጣት እንዲሁም የተጎጂዎችን መፍትሔ የማግኘት መብትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሁሉን አቀፍ ብሔራዊ የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ ተግባራዊ መደረግ አለበት
የመሬት መብት ከምግብ፣ ከጤና፣ ከመጠለያ፣ ከውሃ፣ ከባህላዊ መብቶች ጋር ጥብቅ ግንኙነት ያለው በመሆኑ መሬት ነክ ድንጋጌዎችና ፖሊሲዎች ሰብአዊ መብቶች መር ሊሆኑ ይገባል
All are entitled to equal protection against any discrimination in violation of this Declaration and against any incitement to such discrimination
ሰዎች ሁሉ በሕግ ፊት እኩል ናቸው፤ ያለምንም ልዩነት እኩል የሕግ ጥበቃ የማግኘት መብት አላቸው
መንግሥት በአፋር ክልል በዞን ሁለት፣ በዞን አራት እንዲሁም በሰመራ ከተማ ለሚገኙ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች እና ተመላሾች በቂ፣ ወቅቱን የጠበቀ እና ተደራሽ የሆነ የሰብአዊ ድጋፍ የማቅረብ ኃላፊነቱን በተገቢው መንገድ መወጣት አለበት
ስምምነቱ “የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲው የሲቪክ ማኅበራትን ጨምሮ ከሁሉም ባለድርሻ አካላት በሕዝባዊ ምክክር የሚገኙ ግብአቶችን መሠረት አድርጎ እና መደበኛ ሀገራዊ የፖሊሲ አወጣጥ ሂደቶችን ተከትሎ ሊዘጋጅ እንደሚገባ” ያስቀምጣል
«ታጣቂዎቹ ጥቃቱን ባደረሱበት ከተማ ከማኅበረሰቡ ጋር ተቀላቅለው የሚኖሩ ተፈናቃዮችን ቤትለቤት እየዞሩ በተለይ የአማራ ብሔር ተወላጆችን ለይተው ገድለዋል» በማለት የምርመራ ግኝቱ ጠቁሟል
በወልቂጤ ከተማ ለውሃ አቅርቦት ጥያቄ አደባባይ በወጡ ነዋሪዎች ላይ ያልተመጣጠነ፤ ኃይል ተጠቅሞ ጥቃት በማድረስ ሕይወት እንዲጠፋና የአካል ጉዳት እንዲደርስ ያደረጉ የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ተጠያቂ እንዲሆኑ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አሳሰበ
ተመሳሳይ ዓይነት የመብት ጥሰቶች እንዳይፈጸሙ ለጸጥታ ኃይሎች ግልጽ አመራር ማስተላለፍ ያስፈልጋል
ኮሚሽኑ ያወጣው የምርመራ ዘገባ እንደሚያሳየው ከተገደሉት ሰዎች መካከል 42ቱ በተፈናቃዮች የመጠለያ ጣቢያ ውስጥ እና ከተቀባይ ማኅበረሰብ ጋር ተቀላቅለው ይኖሩ የነበሩ ተፈናቃዮች እንዲሁም መንግሥትን ይደግፋሉ የተባሉ ነዋሪዎች ነበሩ