Skip to content
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Ethiopian Human Rights Commission – EHRC
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
        • Regions

          EHRC is an independent federal institution tasked with the promotion and protection of human rights in Ethiopia.

        • Addis Ababa
        • Afar
        • Amhara
        • Benishangul Gumuz
        • Gambella
        • Oromia
        • Somali
        • Tigray
        • Central Ethiopia
        • Dire Dawa
        • Harari
        • Sidama
        • South Ethiopia
        • South West Ethiopia Peoples'
  • Areas of Work
        • Areas of Work

          We are an independent national human rights institution tasked with the promotion & protection of human rights in Ethiopia.

        • Economic, Social & Cultural Rights
        • Civil & Political Rights
        • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
        • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
        • Women’s & Children’s Rights
        • Human Rights Education
        • Human Rights Monitoring & Investigation
        • Human Rights Film Festival
        • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
 
Ethiopian Human Rights Commission – EHRCEthiopian Human Rights Commission – EHRC

የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ አዋጅ እና ሰብአዊ መብቶች

August 12, 2023August 28, 2023 Press Release

ከአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታው ጥብቅ አስፈላጊነት፣ ተመጣጣኝነት በተጨማሪ የፓርላማው የአስቸኳይ ጊዜ ወቅት ክትትል (Parliamentary Oversight) እና የኮሚሽኑ የሰብአዊ መብቶች ክትትል የማድረግ ኃላፊነት ሊረጋገጥ ይገባል

Twitter Facebook Telegram Email Whatsapp Download Download Print

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ሐምሌ 28 ቀን 2015 ዓ.ም. በሚኒስትሮች ምክር ቤት የታወጀውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቁጥር 6/2015 ላይ ያዘጋጀውን ባለ 26 ገጽ የሰብአዊ መብቶች ትንታኔ እና ዝርዝር ምክረ ሐሳቦች ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መላኩን አስታወቀ፡፡ በመጪው ሰኞ ነሐሴ 8 ቀን 2015 ዓ.ም. በአዋጁ ላይ ለመምከርና ለመወሰን አስቸኳይ ስብሰባ የጠራው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኮሚሽኑን ምክረ ሐሳቦች በጥንቃቄ አጢኖ ተግባራዊ እንዲያደርጋቸው ኮሚሽኑ ጠይቋል፡፡

ኮሚሽኑ ለምክር ቤቱ በላከው የትንታኔ ሰነድ ላይ እንደተመለከተው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ፣ በተለይም በአዋጁ የተመለከቱ ክልከላዎችና ግዴታዎች፣ ለመንግሥት የተሰጠው የአስቸኳይ ጊዜ ሥልጣን፣ የአዋጁ ከባቢያዊና የጊዜ ተፈጻሚነት ወሰን፣ የሕዝብ ተወካዮች እና ዳኞችን ያለምክር ቤቱ ውሳኔ አለመያዝና መከሰስ ልዩ መብት (Immunity) ጨምሮ ሌሎችም ሊገደቡ ስለማይችሉ መብቶች ጥበቃ፤ በአጠቃላይ የአዋጁ እያንዳንዱ አንቀጾች ከጥብቅ አስፈላጊነት (necessity)፣ ተመጣጣኝነት (proportionality) እና ሕጋዊነት (legality) አንጻር አንዲመረመሩ ይጠይቃል፡፡

በተጨማሪም አዋጁ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ በነበሩት ተከታታይ ቀኖች በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ተከስቶ የነበረው የሰላምና ደህንነት ልዩ አደጋ በአሁኑ ወቅት ተወግዶና መደበኛ እንቅስቃሴዎች ወደ ነበሩበት ሁኔታ መመለስ መጀመራቸው በመንግሥት በይፋ የተገለጸ በመሆኑ፤ ምክር ቤቱ በአሁኑ ወቅት የአስቸኳይ ጊዜ ሥልጣን አስፈላጊነት፣ ከባቢያዊና የጊዜ ተፈጻሚነት ወሰንን በተለይ በጥንቃቄ በማጤን ምክር ቤቱ አዋጁን የሚያጸድቀው ቢሆን የጊዜ ተፈጻሚነቱ ከአንድ ወር ወይም የተወሰኑ ሳምንታት የበለጠ እንዳይሆንና ከባቢያዊ ተፈጻሚነቱም ልዩ አደጋው ተከስቷል በተባለበት ቦታ ብቻ የተገደበ እንጂ በጠቅላላ ሀገሪቱ እንዳይደረግ ኮሚሽኑ ምክረ ሐሳብ አቅርቧል፡፡

ኮሚሽኑ የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ አዋጁን አስመልክቶ አዋጁ በተነገረበት ሐምሌ 28 ቀን 2015 ዓ.ም፣ ባወጣው መግለጫ፣ በአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ ውስጥም ቢሆን ሰብአዊ መብቶች ሊከበሩ እንደሚገባ አሳስቦ፤ በተለይም ከሚያዝያ ወር 2015 ዓ.ም. በአማራ ክልል እየተባባሰ ለመጣው የትጥቅ ግጭት እና የጸጥታ ችግር ዘላቂ እና ሰላማዊ መፍትሔ የማፈላለግ ጥረት እንዲቀድም ጥሪ ማቅረቡ የሚታወስ ነው። ኮሚሽኑ ከሚያደርገው መደበኛ የሰብአዊ መብቶች ክትትል በተጨማሪም በተለይ በአስቸኳይ ጊዜ ወቅት የሰብአዊ መብቶች ሁኔታን ክትትል እንዲያደርግ በማቋቋሚያ አዋጁ ሥልጣንና ኃላፊነት የተሰጠው በመሆኑ የአዋጁን አፈጻጸም በሕገ መንግሥቱና ኢትዮጵያ ተቀብላ ባጸደቀቻቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶችና በተለይም የጥብቅ አስፈላጊነት፣ በማናቸውም ሁኔታ የማይገደቡ መብቶችን የመጠበቅ፣ የተመጣጣኝነት እና ከመድልዎ ነጻ መሆን መርሖችን ባከበረ መልኩ መተግበራቸውን በመከታተል ላይ ነው።

ኢሰመኮ በተለያዩ ወቅቶች በሀገሪቱ በከፊልም ሆነ በሀገር አቀፍ የተጣሉ የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታዎች ክትትል እና ምርመራ አድርጎ፣ ሪፖርቱን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና ለሕዝብ ይፋ ማድረጉ የሚታወስ ነው። በአዋጅ ቁጥር 6/2015 ላይ የቀረቡ ምክረ ሐሳቦችም በዋነኝነት በእነዚህ የክትትል እና የምርመራ ግኝቶቹ ላይ የተመሠረቱ ሲሆን፣ በተለይም ከእዚህ ቀደም በነበሩ የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታዎች ወቅት የተለያዩ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች መድረሳቸውንና ከእነዚህም ውስጥ አሳሳቢ ከነበሩ ጉዳዮች ውስጥ ኢሰብአዊ አያያዞች፣ በተለይም በጥቆማ ላይ የተመሠረቱ እስሮችን በተመለከተ የጥቆማዎቹ መነሻ የሰዎቹ የብሔር ማንነት አለመሆኑን ለማረጋገጥ እና ምክንያታዊ ጥርጣሬ ስለመኖሩ ለማጣራት በቂ ጥረት ያልተደረገባቸው በርካታ እስሮች እንደነበሩ፣ ሴቶች፣ አረጋውያን እና አካል ጉዳተኞች እና በመገናኛ ብዙኃን ባለሞያዎች ላይ የደረሱ ጥሰቶችን እንደሚጨምር አመላክቷል።

ኮሚሽኑ በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥትና በዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ስምምነቶችና የሰብአዊ መብቶች መርሖች ላይ በመመሥረት ባቀረበው ትንታኔ ላይ ምክር ቤቱ አዋጁን የሚያጸድቀው ቢሆን ለትርጉም አሻሚ የሆኑና ተለጥጠው በመተግበር ተገቢ ላልሆነ አፈጻጸምና የሰብአዊ መብቶች አደጋ ሊሆኑ የሚችሉ ድንጋጌዎች ላይ ሊደረጉ የሚገባቸውን ማሻሻያዎች በዝርዝር በማቅረብ ምክረ ሐሳብ ሰጥቷል፡፡

የአስቸኳይ ጊዜ አወጁ ጋር የሚቃረኑ የፍሬ ነገር እና የሥነ ሥርዓት ሕጎች በጅምላ መታገዳቸው እና የዲፕሎማቲክ ልዩ መብቶችን ብቻ ሲቀር ሌሎች ከልዩ ሥራና ኃላፊነት ነጻነትን ከመጠበቅ አስፈላጊነት የሚመነጩ ልዩ መብቶቸንና ጥበቃዎችን (Functional Immunity) ሊታገዱ መቻላቸው ከሚያስከትላቸው ውጤቶች መካከል አንዱ ለምሳሌ የፓርላማ አባላትና የዳኞችን ያለ ምክር ቤቱ ውሳኔ ያለመያዝና ያለመከሰስ መብቶችን ጭምር አላግባብ ለማገድ በር የሚከፍት በመሆኑ ይህም በአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ ውስጥም ቢሆን

ሊታገድ የማይችለውን የዳኝነት ዋስትና እና በነጻነት ላይ የተመሠረተ የፍትሕ አስተዳደርን የሚያግድ፣ እንዲሁም በተለይም በአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ ውስጥ ሊደረግ የሚገባውን የፓርላማ ክትትል (Parliamentary Oversight) መርሕ ተፈጻሚነት ሊያደናቅፍ የሚችል ነው፡፡ በማናቸውም ጊዜ ብቁ ነጻ እና ገለልተኛ የዳኝነት አካላት እና የፍትሕ ሥርዓት መኖር ለሕጋዊነት እና ለሕግ የበላይነት መርሖች መተግበር የግድ የሚል ነው፡፡

በአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታም የዳኝነት ተቋሙ ተግባርና ኃላፊነት በሙሉ ነጻነት ሊቀጥል የሚገባው ሲሆን በተለይም የመንግሥት ኃላፊዎች እና የሕግ አስፈጻሚ አካላት የአስቸኳይ ጊዜ ሥልጣን አጠቃቀም ከአስቸኳይ ጊዜ ሕጉ ጋር የሚስማማ መሆኑንና አለመሆኑን፤ እንዲሁም የአስቸኳይ ጊዜ ሥልጣን አተገባበር አላስፈላጊና ተመጣጣኝ ባልሆነ ሁኔታ በሕገ መንግሥቱና በዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ሕግጋት የተረጋገጡ መብቶችን የሚጥሱ መሆናቸውን ወይም አለመሆናቸውን በነጻነት መወሰን መቻል ስላለበት፣ እንዲሁም የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤቱ የአስቸኳይ ጊዜ ወቅት ክትትል (Parliamentary Oversight) እና የኮሚሽኑ የሰብአዊ መብቶች ክትትል በነጻነት መቀጠል ስላለበት፤ የዳኞችና የምክር ቤት አባሎችን ልዩ መብት ጥበቃ ማረጋገጥ አስፈላጊ መሆኑን የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ አሳስበዋል፡፡


ኮሚሽኑ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የላከውን የሰብአዊ መብቶች ትንታኔ ሙሉ ሰነድ እዚህ ያገኛሉ፡፡

ኮሚሽኑ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ወቅት ሊከበሩ ስለሚገባቸው የሰብአዊ መብቶች መርሖች ያወጣውን ሰነድ እዚህ ያገኛሉ፡፡

Related posts

February 15, 2022August 28, 2023 EHRC Quote
ኢሰመኮ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲነሳ የቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ የተወካዮች ም/ቤት ማፅደቁን ተከትሎ በእስር ላይ ያሉ ሰዎች እንዲለቀቁ ጠየቀ
January 26, 2022August 28, 2023 EHRC Quote
ኢሰመኮ የኢፌዲሪ ሚኒስትሮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲነሳ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀረበው የውሳኔ ሃሳብ አበረታች እርምጃ መሆኑን ይገልጻል
August 4, 2023August 28, 2023 Press Release
በአማራ ክልል ያለውን አሳሳቢ የጸጥታ ሁኔታ በተመለከተ
December 15, 2021December 15, 2021 EHRC Quote
የሚዲያ አባላት መታሰር

Signup for the Latest Update from EHRC

Submit your email to singup
Facebook Like us on FacebookXFollow us on XYouTube Follow us on YouTubeLinkedin Follow us on LinkedinWhatsApp WhatsAppTikTok TikTokTelegram TelegramInstagram InstagramFlicker Flickr

Useful Links

  • NANHRI
  • GANHRI
  • OHCHR
  • ACHPR
  • TRANSITIONAL JUSTICE

Get Involved

  • Jobs
  • Events
  • Contact Us
  • Telegram Bot
  • Subscribe to our newsletter

Connect with Us

  • Facebook
  • Twitter
  • LinkedIn
  • YouTube
  • Flickr
  • Instagram
Descriptive Text

We are an independent
national human rights
institution tasked with
the promotion and protection of human
rights in Ethiopia.

Submit your email to get the latest update from EHRC

Address: Sunshine Tower No. 5, Meskel Square, on Bole Road next to Hyatt Regency Hotel, Addis Ababa, Ethiopia
Tel: +251115504031 | Fax: +251 11 550 4125 | PO Box 1165 Addis Ababa | Email: info@ehrc.org


The contents of this website, excepting third party content for which the Commission bears no responsibility,
may be freely used and copied for educational and other non-commercial purposes, provided that any such reproduction is accompanied by an acknowledgement of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC). Source of images used in the content of this website: EHRC Media and Communications Department Archive and Creative Common License.

This website is managed by the Media and Communications team of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC).

We are using cookies to give you the best experience on our website.

You can find out more about which cookies we are using or switch them off in .

Scroll to top
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
    • Addis Ababa
    • Afar
    • Amhara
    • Benishangul Gumuz
    • Central Ethiopia
    • Dire Dawa
    • Gambella
    • Harari
    • Oromia
    • Sidama
    • Somali
    • South Ethiopia
    • South West Ethiopia Peoples’
    • Tigray
  • Areas of Work
    • Economic, Social & Cultural Rights
    • Civil & Political Rights
    • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
    • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
    • Human Rights Monitoring & Investigation
    • Women’s & Children’s Rights
    • Human Rights Education
    • Human Rights Film Festival
    • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Search
Ethiopian Human Rights Commission - EHRC
Powered by  GDPR Cookie Compliance
Privacy Overview

This website uses cookies so that we can provide you with the best user experience possible. Cookie information is stored in your browser and performs functions such as recognising you when you return to our website and helping our team to understand which sections of the website you find most interesting and useful.

Strictly Necessary Cookies

Strictly Necessary Cookie should be enabled at all times so that we can save your preferences for cookie settings.

If you disable this cookie, we will not be able to save your preferences. This means that every time you visit this website you will need to enable or disable cookies again.