Skip to content
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Ethiopian Human Rights Commission – EHRC
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
        • Regions

          EHRC is an independent federal institution tasked with the promotion and protection of human rights in Ethiopia.

        • Addis Ababa
        • Afar
        • Amhara
        • Benishangul Gumuz
        • Gambella
        • Oromia
        • Somali
        • Tigray
        • Central Ethiopia
        • Dire Dawa
        • Harari
        • Sidama
        • South Ethiopia
        • South West Ethiopia Peoples'
  • Areas of Work
        • Areas of Work

          We are an independent national human rights institution tasked with the promotion & protection of human rights in Ethiopia.

        • Economic, Social & Cultural Rights
        • Civil & Political Rights
        • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
        • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
        • Women’s & Children’s Rights
        • Human Rights Education
        • Human Rights Monitoring & Investigation
        • Human Rights Film Festival
        • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
 
Ethiopian Human Rights Commission – EHRCEthiopian Human Rights Commission – EHRC

አፋር ክልል: የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች እና ተመላሾች በዘላቂነት እንዳይቋቋሙ ተግዳሮት ከሆነው የኢኮኖሚ እና የንግድ እንቅስቃሴ ገደብ ጋር የተገናኙ ችግሮች ሊቀረፉ ይገባል

February 22, 2023February 22, 2023 Press Release

መንግሥት በአፋር ክልል በዞን ሁለት፣ በዞን አራት እንዲሁም በሰመራ ከተማ ለሚገኙ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች እና ተመላሾች በቂ፣ ወቅቱን የጠበቀ እና ተደራሽ የሆነ የሰብአዊ ድጋፍ የማቅረብ ኃላፊነቱን በተገቢው መንገድ መወጣት አለበት

Twitter Facebook Telegram Email Whatsapp Print

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በአፋር ክልል በዞን ሁለት (ኪልበቲ ረሱ)፣ በረሐሌ፣ አብአላ እና መጋሌ ወረዳዎች በሚገኙ በ6 መጠለያ ጣቢያዎች፤ በሰመራ ከተማ በሰመራ ስታዲየም ውስጥ የሚኖሩ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች እንዲሁም በዞን አራት (ፈንቲ ረሱ) በጉሊና፣ ያሎ ወረዳዎች እና በዞን ሁለት አብአላ ወረዳ ጉቤ ቀበሌ የሚገኙ ተመላሾች የሰብአዊ መብቶች አያያዝ ሁኔታ ላይ ከኅዳር 10 ቀን 2015 ዓ.ም. እስከ ታኅሣሥ 1 ቀን 2015 ዓ.ም. ክትትል አከናውኗል።

የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች በመፈናቀል ሂደት የቤተሰብ አባሎች ሞት፣ አካል ጉዳት እና ድብደባን ጨምሮ የተለያዩ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት የደረሰባቸው መሆኑን፤ ቤቶቻቸው፣ ንብረቶቻቸው እና ከብቶቻቸው መውደማቸውንና መዘረፋቸውን ለኮሚሽኑ አስረድተዋል። የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ምዝገባ እና ሰነድን በሚመለከት፤ ሰዎች ከመፈናቀላቸው በፊት በቀበሌው የሚገኘውን የነዋሪ ብዛት መጠን በቤተሰብ ደረጃ መረጃ ከመያዝ ባሻገር በመጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ ለሚኖሩ ተፈናቃዮች እና ተመላሾች ምዝገባ እንዳልተከናወነ እና የወሳኝ ኩነት ምዝገባን ጨምሮ ሌሎች ሰነዶችን የመስጠት አገልግሎት አለመጀመሩን ኮሚሽኑ በክትትሉ ለማወቅ ችሏል፡፡

በተጨማሪም በትግራይ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች የሚኖሩ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ዳግም ግጭት ሊከሰት ይችላል የሚል ሥጋት እንዳለባቸው የገለጹ ሲሆን፤ የጦርነት ቀጠና የነበሩ እንደ ጉሊና ወረዳ ፎኪሳ ቀበሌ ባሉ አካባቢዎች ፈንጂ እና መሰል የጦር መሣሪያዎችን በማምከን አካባቢውን ከአደገኛ የጦር መሳሪያዎች የማጽዳት ሥራ በአግባቡ ባለመከናወኑ በተመላሾች ላይ የደኅንነት ሥጋት ፈጥሮባቸዋል፡፡

ክትትል በተደረገባቸው አካባቢዎች ተመላሾች በራሳቸው ሙሉ ፈቃድ የተመለሱ ቢሆንም፤ መደበኛ ኑሯቸውን ለመቀጠል የሚያስችላቸውን ምቹ ሁኔታ በመፍጠር ለተፈናቃዮች ዘላቂ መፍትሔ ማፈላለግን በተመለከተ ክፍተቶች እንዳሉ የኮሚሽኑ ክትትል ያመላክታል፡፡ ከሰሜኑ ጦርነት ጋር በተያያዘ ከሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች በአፋር ክልል ዞን ሁለት እና ዞን አራት በኩል በየብስ ትራንስፖርት ወደ ትግራይ ክልል ተጓጉዘው ይገቡ የነበሩ ነዳጅን ጨምሮ የተለያዩ መሠረታዊ የፍጆታ ዕቃዎች እንዳይገቡ የተጣለው እገዳ ባለመነሳቱ በሁለቱ ዞኖች ውስጥ የሚደረገውን የንግድ እንቅስቃሴ ከመገደቡ በተጨማሪ በፍጆታ ዕቃዎች ላይ ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ አስከትሏል። ይህም በአካባቢው ለተደጋጋሚ መፈናቀል የተዳረጉ ነዋሪዎች በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ሲካሄድ የቆየው ግጭት ካስከተለባቸው የሰብአዊ ቀውስ በተጨማሪ በቂ እና ወቅቱን የጠበቀ የሰብአዊ ድጋፍ ካለመቅረቡ በተጨማሪ የንግድ እንቅስቃሴው ገደብ ባለመነሳቱ ምክንያት እየደረሰባቸው ያለው ያልተገባ ኢኮኖሚያዊ ጫና፤ ተፈናቃዮች እና ተመላሾች በዘላቂነት እንዲቋቋሙ አስቻይ ሁኔታዎች እንዳይፈጠር ተግዳሮት ሆኗል።

ኢሰመኮ ባከናወነው ክትትል የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችና ተመላሾች በቂ፣ ወቅቱን የጠበቀ እና ተደራሽ የሆነ ምግብ፣ ውሃ፣ መጠለያ፣ የጤና አገልግሎት፣ ትምህርት እና ሌሎች ማኅበራዊ አገልግሎቶችን ያካተተ የሰብአዊ ድጋፍ እየቀረበላቸው እንዳልሆነ ተመልክቷል፡፡ በተለይ በጦርነቱ ወቅት የሕክምና ቁሳቁሶች፣ የመድኃኒቶች እና የክትባት ማስቀመጫ ፍሪጅን ጨምሮ በርካታ የጤና አገልግሎት ተቋማት በመዘረፋቸውና በመውደማቸው የሕክምና ቁሳቁስ እና መድኃኒት እጥረት ፈጥሯል። በተመሳሳይ ልዩ ጥበቃ እና ድጋፍ ለሚሹ ተፈናቃዮች ማለትም ለሚያጠቡ እናቶች፣ ነፍሰጡሮች፣ ሕፃናት፣ አካል ጉዳተኞች፣ አረጋውያን እና ተጓዳኝ ሕመም ላለባቸው ተፈናቃዮች የመብቶች ጥሰት ተጋላጭነታቸውን እና ልዩ ፍላጎታቸውን መሠረት ያደረገ የሰብአዊ ድጋፍ እንደማይቀርብ፣ ለሕፃናት እና አጥቢ እናቶች የሚሰጥ የተለየ የምግብ ድጋፍ ስለሌለ ለምግብ እጥረት የተጋለጡ መኖራቸውን ኮሚሸኑ ባደረገው ክትትል ተገንዝቧል፡፡

ኮሚሽኑ ክትትል በተደረገባቸው አካባቢዎች የነበረውን አሳሳቢ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ከለየ በኋላ ጉዳዩ ለሚመለከታቸው የፌዴራል እና የክልል መንግሥት ተቋማት የሁኔታውን አሳሳቢነት የሚገልጽ በተለይ የሰብአዊ ድጋፍ አቅርቦትን እና የዘላቂ መፍትሔ ማፈላለግን በተመለከተ የተስተዋሉ ክፍተቶች እንዲታረሙ በቃል እና በጽሑፍ ምክረ ሐሳቦችን በማጋራት ሁኔታው እንዲሻሻል ሲወተውት ቆይቷል፡፡ በዚህ መሠረት በኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን እንዲሁም በአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት አደጋ ሥጋት አመራርና የምግብ ዋስትና ኮሚሽን አስተባባሪነት ክትትሉ በተደረገባቸው አካባቢዎች ለሚኖሩ ተፈናቃዮች ምግብ እና ምግብ-ነክ ያልሆኑ የሰብአዊ ድጋፎች እንደቀረቡ ለኮሚሽኑ ገልጸዋል፡፡ ይሁንና ኢሰመኮ በድጋሚ ባደረገው ማጣራት ለተፈናቃዮች የተሰራጩ የሰብአዊ ድጋፎች በቂ፣ ወቅቱን የጠበቀ እና ተደራሽ ባለመሆናቸው በተፈናቃዮች ሁኔታ ላይ ተጨባጭ መሻሻል አለመኖሩን ለማወቅ ተችሏል፡፡

የኢሰመኮ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ “በክልሉ የሚገኙ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች የሰሜኑ ጦርነት ካስከተለባቸው የሰብአዊ ቀውስ በአግባቡ ለማገገም እና እራሳቸውን ችለው ለመኖር በሚያደርጉት ጥረት የንግድ እንቅስቃሴ ገደቡ አለመነሳቱ ተጨማሪ የኢኮኖሚ ጫና እየፈጠረባቸው እና መደበኛ ኑሯቸውን እንዳይቀጥሉ ከማድረጉ ባሻገር በዘላቂነት እንዳይቋቋሙ እንቅፋት ሆኗል” ሲሉ በአጽንዖት ገልጸዋል። አክለውም “የፌዴራል እና የክልሉ መንግሥታት እንደአስፈላጊነቱ ለጋሽ ድርጅቶችን በማስተባበር እየተሰጠ ያለውን ሰብአዊ ድጋፍ በማጠናከር ልዩ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው ተፈናቃዮችን ታሳቢ ያደረገ የሰብአዊ ድጋፍ እንዲቀርብ፤ እንዲሁም በክልሉ የሚገኙ ተፈናቃዮችን በዘላቂነት ለማቋቋም የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች እንዲፈጠሩ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሊረባረቡ ይገባል” ሲሉ አሳስበዋል።

Related posts

July 21, 2023August 26, 2023 EHRC Quote
ከፍተኛ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች በሚገኙባቸው ክልሎች እየተባባሰ የመጣውን ሰብአዊ ቀውስ በተመለከተ
October 27, 2023October 31, 2023 Press Release
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ጥቅምት 15 ቀን 2016 ዓ.ም. የኮሚሽኑን 2ኛ ዓመታዊ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች መብቶችን ሁኔታ በተመለከተ ያወጣውን መግለጫ በተመለከተ
August 17, 2023August 18, 2023 Event Update
የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች በሚመለከቷቸው ጉዳዮች ላይ የመሳተፍ መብት አላቸው
June 7, 2021February 12, 2023 Report
ብዛት ያላቸው ተፈናቃዮች ከግንቦት 16 ቀን 2013 ጀምሮ በጸጥታ ኃይሎች ተይዘዋል

Signup for the Latest Update from EHRC

Submit your email to singup
Facebook Like us on FacebookXFollow us on XYouTube Follow us on YouTubeLinkedin Follow us on LinkedinWhatsApp WhatsAppTikTok TikTokTelegram TelegramInstagram InstagramFlicker Flickr

Useful Links

  • NANHRI
  • GANHRI
  • OHCHR
  • ACHPR
  • TRANSITIONAL JUSTICE

Get Involved

  • Jobs
  • Events
  • Contact Us
  • Telegram Bot
  • Subscribe to our newsletter

Connect with Us

  • Facebook
  • Twitter
  • LinkedIn
  • YouTube
  • Flickr
  • Instagram
Descriptive Text

We are an independent
national human rights
institution tasked with
the promotion and protection of human
rights in Ethiopia.

Submit your email to get the latest update from EHRC

Address: Sunshine Tower No. 5, Meskel Square, on Bole Road next to Hyatt Regency Hotel, Addis Ababa, Ethiopia
Tel: +251115504031 | Fax: +251 11 550 4125 | PO Box 1165 Addis Ababa | Email: info@ehrc.org


The contents of this website, excepting third party content for which the Commission bears no responsibility,
may be freely used and copied for educational and other non-commercial purposes, provided that any such reproduction is accompanied by an acknowledgement of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC). Source of images used in the content of this website: EHRC Media and Communications Department Archive and Creative Common License.

This website is managed by the Media and Communications team of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC).

We are using cookies to give you the best experience on our website.

You can find out more about which cookies we are using or switch them off in .

Scroll to top
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
    • Addis Ababa
    • Afar
    • Amhara
    • Benishangul Gumuz
    • Central Ethiopia
    • Dire Dawa
    • Gambella
    • Harari
    • Oromia
    • Sidama
    • Somali
    • South Ethiopia
    • South West Ethiopia Peoples’
    • Tigray
  • Areas of Work
    • Economic, Social & Cultural Rights
    • Civil & Political Rights
    • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
    • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
    • Human Rights Monitoring & Investigation
    • Women’s & Children’s Rights
    • Human Rights Education
    • Human Rights Film Festival
    • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Search
Ethiopian Human Rights Commission - EHRC
Powered by  GDPR Cookie Compliance
Privacy Overview

This website uses cookies so that we can provide you with the best user experience possible. Cookie information is stored in your browser and performs functions such as recognising you when you return to our website and helping our team to understand which sections of the website you find most interesting and useful.

Strictly Necessary Cookies

Strictly Necessary Cookie should be enabled at all times so that we can save your preferences for cookie settings.

If you disable this cookie, we will not be able to save your preferences. This means that every time you visit this website you will need to enable or disable cookies again.