Skip to content
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Ethiopian Human Rights Commission – EHRC
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
        • Regions

          EHRC is an independent federal institution tasked with the promotion and protection of human rights in Ethiopia.

        • Addis Ababa
        • Afar
        • Amhara
        • Benishangul Gumuz
        • Gambella
        • Oromia
        • Somali
        • Tigray
        • Central Ethiopia
        • Dire Dawa
        • Harari
        • Sidama
        • South Ethiopia
        • South West Ethiopia Peoples'
  • Areas of Work
        • Areas of Work

          We are an independent national human rights institution tasked with the promotion & protection of human rights in Ethiopia.

        • Economic, Social & Cultural Rights
        • Civil & Political Rights
        • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
        • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
        • Women’s & Children’s Rights
        • Human Rights Education
        • Human Rights Monitoring & Investigation
        • Human Rights Film Festival
        • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
 
Ethiopian Human Rights Commission – EHRCEthiopian Human Rights Commission – EHRC

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በየደረጃው ያሉ የመንግሥት አስፈጻሚ አካላትና ኃላፊዎች ላይ የቅርብ ክትትል በማድረግ ለሰብአዊ መብቶች መከበር አስተዋጽኦ ሊያደርጉ ይገባል ሲል ኢሰመኮ ጥሪ አቀረበ

May 11, 2022August 28, 2023 Press Release

ለሰብአዊ መብቶች ጥሰት ተጠያቂነትን በማረጋገጥ፣ የሕግ በላይነትን በማስፈን፣ መንግሥትና የስራ አስፈጻሚ አካላቱ በመሉ ለሰብአዊ መብቶች መከበር፣ መጠበቅና መሟላት ያላቸውን ቁርጠኝነት እንዲያድሱና እንዲተገብሩ ልዩ ትኩረትና ክትትል ይሻል

Twitter Facebook Telegram Email Whatsapp Print

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የ10 ወር የሥራ ክንውን ሪፖርቱን ግንቦት 3 ቀን 2014 ዓ.ም. ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግ፣ የፍትሕ እና የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበበት ወቅት የኮሚሽኑ የአምስት ዓመት የስትራቴጂ እቅድ የመጀመሪያ የትግበራ ዓመት እንደመሆኑ መጠን፣ ዋና ዋና ተግባራት ተብለው ከተለዩ የሰብአዊ መብቶች ሥራዎች ጎን ለጎን በርካታ የተቋም ግንባታ ሥራዎች መከናወናቸውን አስታውሷል። በዚህ ረገድ የኮሚሽኑን አካላዊና ዲጂታል ተደራሽነት የማሻሻል፣ በሰፊ ጥናት ላይ የተመሰረተ አዲስ  መዋቅር በመተግበር ተቋሙን በሰው ኃይል ማብቃት፣ የበጀት ነጻነቱን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ አሰራሮችንና ደንቦችን በመቅረጽና ለሥራው አስፈላጊ የሆነ ሃብት በማሰባሰብ የኮሚሽኑን የፋይናንስ አቅም የማሻሻልና እንዲሁም ከሌሎች አቻ ብሔራዊ የሰብአዊ መብቶች ተቋማትም ሆነ ከአህጉራዊና ከዓለም አቀፍ ድርጅቶች ጋር የተዘረጉ የትብብር ሥራዎች በዝርዝር ቀርበዋል።  

በተጨማሪም በኢሰመኮ ሪፖርት ከተጠቀሱ በክትትልና ምርመራ ሥራዎቹ ባለፉት 10 ወራት ከተከናወኑ ሥራዎች ውስጥ በተለይ ግጭት የተከሰተባቸው 65 ቦታዎችን መድረሱን፣ ባለፉት 3 ወራት ብቻ 450 ሺህ ስደተኞችን የሚያስጠልሉ አስር ስደተኛ ካምፖች ላይ የክትትል ሥራ ማከናወኑን፣ በአምስት ክልሎች የሚገኙ 1.5 ሚልዮን ገደማ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችን የሚያስጠልሉ 47 ጊዜያዊ መጠለያዎች፣ ጣቢያዎችን እና ተቀባይ ማኅበረሰቦችን መጎብኘቱን እና ሪፖርት እና ምክረ ሃሳቦችን እንደየአግባብነቱ በይፋዊ መግለጫ ወይም ጉዳዩ ለሚመለከታቸው አካሎች ማቅረቡ ተገልጿል። 

ነጻነታቸውን የተነፈጉ ሰዎች አያያዝን በተመለከተ፣ በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ 82 ማረሚያ ቤቶች እና በ270 ፖሊስ ጣቢያዎች ላይ የሰብአዊ መብቶች ክትትል ማከናወኑንም ከተጠቀሱት የክትትልና የምርመራ ሥራዎች መካከል ናቸው። 

የኢሰመኮ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ ኮሚሽኑ የተቋማዊ ግንባታን በተመለከተ ያከናወናቸውን ተግባራት  ገለጻ ሲያደርጉ፣ ኮሚሽኑ በዓለም አቀፍ ደረጃ ብሔራዊ የሰብአዊ መብቶች ተቋማት የሚመሩበትና “የፓሪስ መርሆዎች” ተብለው በሚታወቁት መስፈርቶች/መርሆች መሰረት የሚጠበቅበትን ሙሉ በሙሉ በማሟላቱ የደረጃ አንድ (A Status) እውቅና ያገኘው ባለፉት 10 ወራት መሆኑን አስታውሰዋል፡፡

የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ በበኩላቸው ኮሚሽኑ በሪፖርቱ ወቅት ባከናወናቸው ተግባራት አማካኝነት የለያቸውንና ምክር ቤቱ ልዩ ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገባቸውን የሰብአዊ መብቶች ሁኔታዎችንና ምክረ ሃሳቦችንም አቅርበዋል። 

በተለይ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በተከሰተው ጦርነት እንዲሁም በሌሎች የሀገራችን ክፍሎች ከብሔር ማንነት፣ ራስን በራስ የማስተዳደርና የአስተዳደር አካባቢዎች ወሰን አልፎ አልፎም ከሃይማኖት ጥያቄ ጋር በተያያዘ በተለያዩ ወቅቶች በሚያገረሹ ግጭቶች ሳቢያ ጾታዊና ወሲባዊ ጥቃቶችን ጨምሮ እጅግ በርካታ ሰዎች ለሞት፣ ለአካልና ለሥነልቡና ጉዳት፣ ለመፈናቀልና፣ ለንብረት ውድመት መዳረጋቸውን አስምረውበታል። በመሰረተ ልማቶች ላይ በደረሰ ውድመትም መሰረታዊ አገልግሎቶች መቋረጣቸውን፣ ከፍተኛና መጠነ ሰፊ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች መፈጸማቸውን፤ ይህን አይነት የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ስጋትም እንደቀጠለ አስታውሰው፤ በትግራይ ክልል ተጀምሮ ወደ አፋርና አማራ ክልል ተስፋፍቶ የነበረው ጦርነት አሁን ላይ መብረዱና የሰብአዊ እርዳታ አቅርቦት መሻሻሉ ተስፋ ሰጪ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ፤ የሰብአዊ እርዳታ አቅርቦቱ በፍላጎቱ መጠን የተሟላ እንዲሆን፣ መሰረታዊ አገልግሎቶች ወደ ነበሩበት ቦታ እንዲመለሱ፣ ዘላቂ ሰላማዊ መፍትሄና ፍትሕ እንዲረጋገጥ ገና ብዙ እርምጃዎችና ሥራዎች እንደሚቀሩ ገልጸዋል፡፡  

ባለፉት አስር ወራት በተለያዩ ወቅቶች ከሕግ ውጪ የተፈጸሙ ግድያዎች፣ ከመጠን ያለፈ የኃይል አጠቃቀም፣ የዘፈቀደና ከፍርድ ወይም ክስ በፊት ያለ የተራዘመ እስር፣ በጋዜጠኞችና በፖለቲካ ተቃዋሚዎች ላይ ያነጣጠረ እስራት እና የአንዳንድ እስር ቦታዎች አያያዝ ሁኔታ አሳሳቢነት እየጨመረ በመምጣቱ የምክር ቤቱን ልዩ ትኩረት እንደሚሻ ተገልጿል፡፡ 

በጦርነትና በግጭት እንዲሁም በሌሎች ምክንያቶች የተጎዱ የመሰረተ ልማት አውታሮችን መልሶ ከማቋቋም ጎን ለጎን ሀገራዊው ኢኮኖሚያዊ ሁኔታና የኑሮ ውድነት፤ እንዲሁም በልዩ ልዩ ማህበራዊና መንግስታዊ አገልግሎቶች አሰጣጥ የሚሰማው የሕዝብ ቅሬታ ለሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ አደጋና ስጋት በመሆኑ የቅርብ ክትትል የሚሹ ጉዳዮች መሆናቸውም ሪፖርት ተደርጓል። 

ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በማጠቃለያቸው ሁሉም የምክር ቤቱ አባላት፤ በየደረጃው ያሉ የመንግሥት አስፈጻሚ አካላትና ኃላፊዎች ላይ እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎችና ኃላፊዎች ላይ የቅርብ ክትትል በማድረግ፣ በመጠየቅና በማስፈጸም፣ ለሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን አስፈላጊውን ድጋፍና እገዛ በመስጠት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

Related posts

February 21, 2023February 21, 2023 Press Release
ኢሰመኮ ለመጀመሪያ ጊዜ ያከናወነውን የአረጋውያን እንክብካቤ ማእከላት የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ክትትል ሪፖርት ይፋ አደረገ
February 6, 2023August 28, 2023 Press Release
በደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ክልል በሚካሄደው ሕዝበ ውሳኔ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ክትትል የሚያደርግ የባለሙያዎች ቡድን ኢሰመኮ አሰማራ
April 5, 2023August 26, 2023 EHRC Quote
በትግራይ ክልል የሚከናወነውን መደበኛ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ክትትል ሥራ በተመለከተ
February 10, 2021February 11, 2023 Report
የትግራይ ክልል ነዋሪዎች ስለሚገኙበት ወቅታዊ ሁኔታ አጭር የክትትል ሪፖርት

Signup for the Latest Update from EHRC

Submit your email to singup
Facebook Like us on FacebookXFollow us on XYouTube Follow us on YouTubeLinkedin Follow us on LinkedinWhatsApp WhatsAppTikTok TikTokTelegram TelegramInstagram InstagramFlicker Flickr

Useful Links

  • NANHRI
  • GANHRI
  • OHCHR
  • ACHPR
  • TRANSITIONAL JUSTICE

Get Involved

  • Jobs
  • Events
  • Contact Us
  • Telegram Bot
  • Subscribe to our newsletter

Connect with Us

  • Facebook
  • Twitter
  • LinkedIn
  • YouTube
  • Flickr
  • Instagram
Descriptive Text

We are an independent
national human rights
institution tasked with
the promotion and protection of human
rights in Ethiopia.

Submit your email to get the latest update from EHRC

Address: Sunshine Tower No. 5, Meskel Square, on Bole Road next to Hyatt Regency Hotel, Addis Ababa, Ethiopia
Tel: +251115504031 | Fax: +251 11 550 4125 | PO Box 1165 Addis Ababa | Email: info@ehrc.org


The contents of this website, excepting third party content for which the Commission bears no responsibility,
may be freely used and copied for educational and other non-commercial purposes, provided that any such reproduction is accompanied by an acknowledgement of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC). Source of images used in the content of this website: EHRC Media and Communications Department Archive and Creative Common License.

This website is managed by the Media and Communications team of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC).

We are using cookies to give you the best experience on our website.

You can find out more about which cookies we are using or switch them off in .

Scroll to top
  • About
    • Who We Are
    • Our Team
    • Careers
    • Contact Us
  • Regions
    • Addis Ababa
    • Afar
    • Amhara
    • Benishangul Gumuz
    • Central Ethiopia
    • Dire Dawa
    • Gambella
    • Harari
    • Oromia
    • Sidama
    • Somali
    • South Ethiopia
    • South West Ethiopia Peoples’
    • Tigray
  • Areas of Work
    • Economic, Social & Cultural Rights
    • Civil & Political Rights
    • IDPs, Refugees & Migrants’ Rights
    • Rights of Persons with Disabilities & the Rights of Older Persons
    • Human Rights Monitoring & Investigation
    • Women’s & Children’s Rights
    • Human Rights Education
    • Human Rights Film Festival
    • Human Rights Moot Court Competition
  • Press Releases
  • Reports
  • Media
    • EHRC on the News
    • EHRC Newsletters
    • EHRC Videos
    • EHRC Visuals
  • Latest
    • Expert Views
    • Explainers
    • Event Updates
    • Annual Ethiopia Human Rights Situation Reports
  • Resources
Facebook XYouTube Linkedin Flicker TikTok Instagram WhatsApp Telegram
Search
Ethiopian Human Rights Commission - EHRC
Powered by  GDPR Cookie Compliance
Privacy Overview

This website uses cookies so that we can provide you with the best user experience possible. Cookie information is stored in your browser and performs functions such as recognising you when you return to our website and helping our team to understand which sections of the website you find most interesting and useful.

Strictly Necessary Cookies

Strictly Necessary Cookie should be enabled at all times so that we can save your preferences for cookie settings.

If you disable this cookie, we will not be able to save your preferences. This means that every time you visit this website you will need to enable or disable cookies again.