ኢትዮጵያ ባጸደቀቻቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶች እና በሌሎች የኢትዮጵያ ሕጎች በሰው ልጅ ላይ የተፈጸሙ ወንጀሎች ተብለው የተወሰኑትን ወንጀሎች፣ የሰው ዘር የማጥፋት፣ ያለፍርድ የሞት ቅጣት እርምጃ የመውሰድ፣ በአስገዳጅ ሰውን የመሰወር፣ ወይም ኢ-ሰብአዊ የድብደባ ድርጊቶችን በፈጸሙ ሰዎች ላይ ክስ ማቅረብ በይርጋ አይታገድም
ሃይማኖትንና እምነትን የመግለጽ መብት ሊገደብ የሚችለው የሕዝብን ደኅንነት፣ ሰላምን፣ ጤናን፣ ትምህርትን፣ የሕዝብን ሞራል፣ የሌሎች ሰዎችን መሠረታዊ መብቶችና ነጻነቶች ለማስጠበቅ እና መንግሥት ከሃይማኖት ነጻ መሆኑን ለማረጋገጥ በሚወጡ ሕጎች ይሆናል
Freedom to express or manifest one's religion or belief may be subject only to such limitations as are prescribed by law and are necessary to protect public safety, peace, health, education, public morality or the fundamental rights and freedoms of others, and to ensure the independence of the state from religion
ሴቶችና ሕፃናትን በተመለከተ የሚከናወኑ የውትወታ ሥራዎች ስልታዊና ሰብአዊ መብቶች ተኮር ሊሆኑ ይገባል
በዚህ ጉዳይ ላይ በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሲቪልና የፖለቲካ እንዲሁም የማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ መብቶች ኮሚሽነር ዶ/ር አብዲ ጅብሪል ለብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት፥ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያዉን ተከትሎ ለግል ድርጅት ተቀጣሪ ሰራተኞችም የደሞዝ ማሻሻያ መደረጉ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል
መንግሥት የሠራተኛውን ሕዝብ ጤንነት፣ ደኅንነትና የኑሮ ደረጃ ለመጠበቅ መጣር አለበት
Government shall endeavour to protect and promote the health, welfare and living standards of the working population of the country
በተለይም ሴት ሕፃናት የመማር መብታቸውን ከማጣታቸው አልፎ ለ ያለ ዕድሜ ጋብቻ እና ለሌሎች የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች እንዲሁም ጥቃቶች ተጋላጭ መሆናቸው፣ ወደ ከተማ እየፈለሱና ለጉልበት ብዝበዛ እየተዳረጉ መሆኑን ኮሚሽኑ አመልክቷል
በኢትዮጵያ በተለያዩ ክልሎች ባሉ ግጭቶች እና በሌሎችም ምክንያቶች የተነሳ ከ5500 በላይ ትምህርት ቤቶች የመማር ማስተማር ሥራቸውን ከማከናወን ውጪ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ገለጸ
ኢሰመኮ ትኩረት ሰጥቶ ከሚሠራባቸው የሰብአዊ መብቶች ዘርፎች መካከል በፖሊስ ጣቢያዎች እና በማረሚያ ቤቶች የሚገኙ ታራሚዎችን የሰብአዊ መብቶች ጥሰትን በተመለከተ የመከታተልና ጉዳዩ እልባት እንዲያገኝ ከሚመለከተው አካል ጋር እየተነጋገሩ እንደሆነ ከተቋሙ ባገኘነው መረጃ ለማወቅ ተችሏል